Thursday, April 28, 2011

የማህበረ ቅዱሳን አባላት በአንድ ጉዳይ ለሁለት መከፈላቸው ተሰማ(abaselama)

የማህበረ ቅዱሳን አባላት በአንድ ጉዳይ ለሁለት መከፈላቸው ተሰማ

ማህበረ ቅዱሳን ተሃድሶዎችን ለማሳደድ 100000 ብር ያስፈልጋኛል ብሎ ገቢ ለማሰባሰብ እየተዘጋጀ ባለበት ባሁኑ ወቅት ጊዜያችንን እና ገንዘባችንን በማይጠቅም ነገር ላይ ማጥፋት የለብንም የሚሉ አባላት ከውስጥ ተቃውሟቸውን እያነሱ ነው። እነዚህ ተቃዋሚዎች ምክንያታቸውን ሲያቃርቡ በቅርቡ የያዙት ተሃድሶን የማሳደድ ፕሮግራም በሕዝቡ ዘንድ ተቀባይነት ማጣቱና ወጤት ካለማስገኝቱም በላይ በተቃራኒው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ ክርስቲያንን ሕዝብ ለሁለት እየከፈለ ከፍተኛ አለመተማመንን ፈጥሯል ይላሉ።

ብዛት ያላቸው ምዕመናን ደግሞ ቄሶችና ሰባኪዎች ተሃድሶ ከሆኑ እኛስ ከነርሱ በምን እንበልጣለን? ይህ ጉዳይ የካህናቱ ስለሆነ ያናንተን አልባልታ መስማት አንፈልግም በማለት ከፍተኛ ተቃውሞአቸውን በማህብረ ቅዱሳን ላይ አሰምተዋል እያሰሙም ነው።
በዋናነት ግን ማህበረ ቅዱሳንን ለሁለት ለመከፈል ያበቃው የገረገራ ጊዮርጊስ ጉዳይ ነው። ባለፈው እንደ ዘገብነው የሰሜን ወሎ ስራ አስኪአጅን ጨምሮ አራቱ የማህበረ ቅዱሳን አባላት ኢየሱስ ክርስቶስን ሲያሳድዱ ሰንብተው ሲመለሱ የጌታ ቁጣ እንዳገኛቸውና አጥንታቸው ተለቅሞ እስኪቀበር ድረስ እንደተቀጡ ይታወቃል። በዚህ የመቂት ወረዳ የማሳደድ ፕሮግራማቸው ወንጌልን እንሰብካለን ብለው ሕዝብን በማታለል ወንጌልን ሲቃወሙ ሰንበተዋል። ሦስት ዲያቆናትን ሁለት ቄሶችን፤ አንድ የቅዳሴ መምህርና የመምሪያ ኃላፊን ከሥራቸው አፈናቅለዋል ሕዝብ በድንጋይ እንዲወግራቸው ቅሥቀሣ አድርገዋል በዚህም ምክንያት እነዚህ አገልጋዮች በገንዛ ሐገራቸው እንዳይወጡ እንዳይገቡ በመንገድ ላይ እንኳ እንዳይታዩ ተደርገዋል. ዘመድ እና ወገን እንዲአይገላቸው ማህበረ ቅዱሳን በመቀስቀሱ ከፍተኛ ስደት ደርሶባቸው ዛሬ በሥጋት ላይ ይገኛሉ።
ጌታ ግን የመውጊያውን ብረት ብትቃወመው ባንተ ይብስብሃል እንዳለው የመውጊያውን ብረት የተቃወሙት አራት የማህበረ ቅዱሳን ባላት በመውጊያው ተወግተው ወደ ማይመለሱበት ዓለም ሄደዋል። ይህ ነገር ግን የገረገራን ሕዝብና ማህብረ ቅዱሳንን ለሁለት ከፈለ። ግማሹ የገረገራ ሕዝብ የማህበረ ቅዱሳን አባላት ኃጢአተኛ ናቸው ቅዱሳንን ስላሳደዱ ወዲያው ፍርዳቸውን አገኙ እነዚህ ቄሶች እውነተኛ የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋዮች ነበሩ እናም ወደ ቦታቸው መመለስ አለባቸው በማለት በመከራከር ላይ ይገኛል።
ግማሹ የድጋይ ልብ የያዘው የገረገራ ሕዝብ ግን በነዚህ ሰዎች ምክንያት ነው ወንድሞቻችን አደጋ የደረሰባቸውና እነዚህን ቄሶች መበቀል አለብን ብሎ ቄሶችን ለመግደል በፈለግ ላይ ነው። ለንስሐ መዘጋጀት ይቅርታ መጠየቅ ሲገባ እንደገና ቄሶችን ከተሰደዱበት ፈልጎ ለመግደል መሞከር በጣም የሚያሳዝን ነው። ጌታ የሚገላችሁ ሁሉ እግዚአብሔርን እንደሚያገለግል የሚመስልበት ጊዜ ይመጣል ያለው ቃል እየተፈጸመ ነው። ነገሩን ላስተዋለው ግን ይህ ጉዳይ ለማህበረ ቅዱሳን የንስሐ ጥሪ መሆኑን ነው። ኢየሱስን በማሳደድ አንድም ሰው አልተጠቀመም።
የገረገራ ሕዝብ የመከፋፈሉን ያህል የማህበረ ቅዱሳን አባላትም ጥቂቶቹ የወንድሞቻቸው በአደጋ መሞት በጥሞና ሥራቸውን እንዲመረምሩ አድርጓቸዋል። ማንን እያገለገልን ይሆን? የሚሉ አባላት በዝተዋል እነዚህ እግዚአብሔር የድንጋዩን ልብ አውጥቶ የሥጋና የመንፈስ ልብ የሰጣቸው ናቸው በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ እንደተባለው ራሳቸውን የሚመረምሩ እየበዙ ናቸው
አንዳዶች ይህ ቅጣት ከእግዚአብሔር የተላከልን ማስጠንቀቂያ ነው እና ነገሮችን እንደገና ማጤን አለብን፤ ሰው ኢየሱስ ክርስቶስን ካመነ በቂው ነው የሚሉ ሐሳቦች በማህበረ ቅዱሳን ዋና ቢሮ እና ንኡስ ማዕከላት ተጧጡፏል።
እነዳንኤል ክብረትና መሰሎቹ ደግሞ እንደ ፈሮን ዓይነት የድንጋይ ልብ እንደተሰጣቸው እንዲያውም ያሁኑ ፕሮግራማችን ካልተሳካ ድብደባ እና ግድያ እንጀምራለን በማለት እየፎከሩ ነው። በተለይም ዳንኤል ክብረት የታባለው የክርስቶስ ጠላት "አባ ሕርያቆስ ከሌሉበት መንግሥተ ሰማያት አባ ሕርያቆስ ያሉበት ሲኦል እንደሚሻለው" ሲናገር ተደምጧል።
አባ ሕርያቆስ የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ጓደኛ ሲሆኑ የዋልባ መነኩሴ በነበሩበት ወቅት ቅዳሴ ማርያምን የደረሱ ሰው እንደነበሩ ድርሳነ ኡራኤል ይናገራል። ነገር ግን ድርሰቱ ከግብጽ የመጣ ለማስመሰል አባ ሕርያቆስ ዘብሕንሳ ተብለው ይጠራሉ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ግን ሰውየውን አታውቃቸውም  የኢትዮጵያው የአባ ሕርያቆስ ቅዳሴም ግብጽ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አይገኝም። እንደ ድርሳነ ኡራኤል ዘገባ ከሆነ ግን ሰውየው ኢትዮጵያዊ ናቸው። ሰውየው የትም ይሁኑ የት ግን ዳንኤል ክብረት ሰውየውን ካላገኘኋቸው ወደ መንግሥተ ሰማያት አልገባም ብሎ እምቢ ያለበት ምክንያት ግልጽ አይደለም። ሰውየው ገና ቅዳሴ ማርያምን ደርሰዋል ብለን አድራሻቸውን ልናውቅ እንችላለንን? ሲኦል ይሁኑ ገነት እንዴት ማረጋገጥ ይቻላል? ብዙ የማያምኑ ሰዎች ጠንቋዮችም ታላላቅ ድርሰት እንዳላቸው የታወቀ ነው። ግሩም ድንቅ የሆኑ ምሥጢራዊ ቅኔዎችን የሚቀኙ ሰዎች ጠንቋይ ሆነው አግኝተናቸዋል። ስለዚህ ያንድ ሰው እውቀታዊ ችሎታ ሲኦል ወይም ገነት ለመግባቱ ማረጋገጫ አይሆንም ይህን ጉዳይ የሚያውቀው እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ዳንኤል የሚሻለውን ራሱ ያውቃል ምርጫው የራሱ ነው እኛ ግን ማንም እዚያ ባይገኝ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለበትን መርጠናል። በእርግጥም የዳንኤሉ አባ ሕርያቆስ ጌታ ባለበት ከተገኙ እኛም እዚያ እናገኛቸዋለን ምን አልባት ከሌሉ ግን እርሳቸውን ተከትለን ሲኦል መግባት አንፈልግም። ለዳንኤል ይመቸው። ይህ ትምህርቱን በሲዲ አሳትሞ ለሕዝብ ማሰራጨቱ ጉዙው ወዴት እንደሆነ ከወዲሁ ማወቅ ይችላል።
ዳንኤል እና መሰሎቹ የሰሜን ወሎው አደጋ የጌታ ቅጣት መሆኑ አልተዋጠላቸውም ይልቁንም የጌታ ቅጣት ነው ብለው ያመኑትን እና ለንስሐ የተዘጋጁትን እናንተም ከሐተሃድሶዎች ጎራ ልትመደቡ ትችላላችሁ የሚለውን የተለመደ ማስፈራሪያ እያስተጋቡ ነው።
ለቤተክርስቲያናችን መሻሻል የምንጥር የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች ግን የወንድሞቻችንን ክፉ ነገር አንመኝም እግዚአብሔር ይቅር እንዲላቸውም እንጸልያለን ክፉውን በክፉ አትቃወም ይላልና ቃሉ ማህበረ ቅዱሳንን በክፉ አናስበውም እርሱ ሊገለን ሊያስድደን በሕዝባችን ፊት ሊያዋርደን ስማችንን ቢያጠፋም ስለ ስሜ ክፉውን ያደርጉባችኋል፣ ስለስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ የሚለው የጌታ ቃል ትዝ ስለሚለን በደስታ ተሞልተናል ወንድሞቻችን በያዙት የተሣሳተ አቋም ግን እጅግ አዝነናል ያዝነውም ስለምንወዳቸው እንጂ ሥራው ተጓጎለ ብለን አይደልም ሥራውን ጌታ እኛ እንደማንሠራው ጠንቅቀን እናውቃለን። እኛ ስለስሙ መነቀፋችን ደስ አሰኝቶናል ሥራው የጌታ ነው ሁሉም በጊዜው ይከናወናል ተሐድሶ የጌታ ሐሳብ ከሆነ ያብባል ይስፋፋል የጌታ ካልሆነ ግን ይጠፋል እኛ ብንሰደድ ኢየሱስ ክርስቶስ ሌሎች የተቀቡ አገልጋዮችን ያስነሳል። እግዚአብሔርን ማሸነፍ አይቻልም፤ ለወንድሞቻችን ለማህበረ ቅዱሳን አባላት የምንመክረው ግን ከማትችሉት ጌታ ጋር ነውና የገጠማችሁት ተጠንቀቁ ነው፤ እኛም ቢያንስ በሀገራችን የመኖር መብት አለን በቤተ ክርስቲያናችንም ጥያቄ የማንሳት መብት አለን መልሱን ግን ከዚያው ከሲኖዶሱ እንጂ ከናንተ አንጠብቅም። እናም እኛን በመግደል ደም ማፍሰስ እንጂ ሌላ ምን ትርፍ ታገኛላችሁ? ፖለቲካ ከሆነ አላማችሁ ለምን ፓርቲ ሆናችሁ አትወዳደሩም? በኛ ደም ለመበልጸግ እኛን በማርከስ ልትቀደሱ አስባችሁ ነው? ለምን አታስተውሉም? ሰውን በማሳደድ የጸደቀ ማን ነው? የሃማኖት ችግር አላባችሁ ካላችሁ ሊቃውንት ጉባኤው መድረክ ያዘጋጅልንና ማን እንደተሣተ እንንወያይ ስንላችሁ እምቢ ከተሐድሶዎች ጋር አብረን አንቀመጥም በማለት ትሸሻላችሁ ፡ ለምን ትሸሻላችሁ? አላውቂነታችሁ እንዳይገለጥ አይደለምን? መወያየት አንፈልግም ካላችሁ ለምን ታሳድዱናላችህ? በእውነት በእግዚአብሔር መንፈስ የምትመሩ ከሆነ አልቧልታ በየመንደሩ ከመንዛት ቃሉን ሰብካችሁ ለምን አታሳምኑንም?
አሁን የያዛችሁት ፕሮግራም ግን ከምር አደገኛ ነው ሕዝቡን ግራ ያጋባና እርስ በርሱ እንዳይተማመን የሚያደርግ ለወንጌልም ልቡን እንዲዘጋ ንስሐ ገብቶ እንዳይፈወስ እያረጋችሁ ነው በዚህ ተንኮላችሁ ምክንያት በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚመጣው የእግዚአብሔር ቁጣ ያስፈራል ቁጣውን ብትንቁ እንኳ ለትውልድ አይብጅምና አስቡበት የጓደኞቻችሁን ሐሳብ ለማዳመጥ ጆሮአችሁን ክፈቱ፤ እኛ ተከፋፍላችሁ እንድትጋደሉ አንፈልግም ግን ተለውጣችሁ ለውጥ እንድታመጡ እንፈልጋለን ይህ ለኛም ለሀገርም ለቤተ ክርስቲያንም ለናንተም ለጌታም ይጠቅማል አሜን
የለውጥ ያለህ?
ታዛቢው ነኝ

እኛም አውቀናል …! ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

እኛም አውቀናል …! ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

 
ለተከበራችሁ በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጭ ለምትገኙ ሴቶችም ወንዶችም ኢትዮጵያውያን!!
በዛሬው ዕለት እጅግ አጠር ባለ መልኩ የዓባይን ጉዳይ በተመለከተ ማናችንም ብንሆን ልንስተው የማይገባ እውነት ላወሳችሁ እወዳለሁ። ይኸውም ኢትዮጵያዊ ሆኖ የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁን ካለበት የደከረተና የከረፋ የባርነት፣ የውርደት፣ የሰደት፣ የረሀብ፣ የጉስቁልና እንዲሁም ከማያባራ የቅሶና የዋይታ ኑሮ ወጥቶ የሰላምና የዕረፍት ሕይወት ይመራ ዘንድ የሚጠላ፤ የኢትዮጵያ ምድር ትንሣኤ የማይዋጥለትና እንደ ኮሶ መድኃኒት የሚከነክነው ፍጥረት አይኖርም! ሊኖርም አይችልም። ሀገራችን ኢትዮጵያ ከ80% በላይ ባለቤት የሆነውን ፈሳሽ ተገድቦ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጠቃሚ ቢሆንና ለውጥ በምድራችንና ብልጽግና በኢትዮጵያ ሕዝብ ቢመጡ የማይዋጥለት ሌላ ማንም ሳይሆን የኢህአዴግ መንግሥት ራሱ ብቻ ነው።
የዚህ ያለ ሕዝብ ይሁንታ በጠመንጃ በሥልጣን ላይ የሚገኘውን መንግሥት የሚደንቅና የሚያሳዝነው ደንባራ ገጽታ አንዱ የተመለከትን እንደሆነ እነሱ ብቻ አዋቂዎች፣ ብልጦች፣ የሚያስቡትንና የሚመክሩትን የላቀና የማይደረስበት ራሳቸውን ከሰው በላይ አድገው ሲወስዱና ሲቆጥሩ በአንጻሩ ደግሞ ሰፊውን ሕዝብ ምንም የማያውቅ የአብርሃም በግ አድርገው መፈረጃቸው ነው። ይሁንና ዛሬ ማለት ትናንት ሊሆን እንደማይችል ከሰው ልጅ በላይ ነፋሳት ምስክርነታቸው አሰምተዋል።
ዓባይ ተገድቦ ለኢትዮጵያ ምድርና ሕዝብ ረብ ይዋል ሲባል የሁላችን ሀገር ወዳድ ዜጎች የላቀ ደስታ ነው። በዚህ ግልጥ ባለ ሀሳብ ላይ አንዱ ከሻሽ ሌላው ተከሳሽ ወይንም ደግሞ አንዱ የጭዋ ሌላው ደግሞ የባርያዋ ልጅ ተብሎ ነገር አይኖርም። ጥያቄው ከሊቅ እስከ ደቂቅ የተቀጣጠለውን እሳት በውስጡ አምቆ ይዞ የማይበጀውና የማይፈልገውን ከትክሻው አሽንቀጥሮ ለመጣል ለለውጥ በለውጥ ትርክ ላይ ለመሮጥ በተጠንቀቅ በቆመበት ሰዓት (በቃ! ለማለት ነው) ዓባይ ዓባይ ማልትስ እኛም አውቀናል … አይስብልም ወይ ጉበዝ? አሁንስ እነዚህ ሰፈርተኞች በማን ደምና ነፍስ ዘመነ ሥልጣናቸውን ያራዝሙ?
እንግዲህ ምን እንላለን በድጥ ላይ የቆማችሁ ሞኞችና ቅሎች ሳላችሁ ተራ ተንኮልና ሴረኝነት እውቀትና ጥበብ ሆኖ ከተሰማችሁና ከመሰላችሁ ዓባይ በማለት የኢትዮጵያ ሕዝብ ልብ ለመስለብ፣ ከገባችሁበት ጉድጓድ ለመውጣት እንደ መሰላል ለመጠቀምና የላላችውን ፈትል ዳግም ለመለቀብ ከሆነ ዓባይ እንደ ባድመ ለተጨማሪ አስር ዓመታት በግርግር የሚያሰነብታችሁ ሳይሆን ስትበቅሉ ጀምሮ እስከ ዛሬው ዕለት የዘራችሁትን ዘር የሚያሳጭዳችሁ ማዕበል ለመሆኑ አትዘንጉ።
በመጨረሻ መንግሥታት ሕዝብን አንድ ሁለት ጊዜ ያታልሉ ይሆናል በሦስተኛው ግን ተራው የሕዝቡ ይሆንና አንድና ሁለት በሌለው ሁኔታ ጭራሽ ለዘልአለም እንደሚሽራቸውና እንደሚቀብራቸው ሳይታለም የተፈታና ፀሐይ ያሞቀው የአደባባይ ምሥጢር ከመሆኑ ባሻገር በተጨማሪ በአንድም በሌላም ምክንያት ያለ እውቀት ከጀርባው ሞት ባለበት አጀንዳ ለተሰለፍን ዜጎች የምለው ነገር ቢኖር እውነት የኢህአዴግ መንግሥት የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመጥቀም ሳይሆን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ፍርድ ለማምለጣና ጠፍተህ ለማጥፋት የጠነሰሰው ሴራ መሆኑ ተገንዝበን በምንም ዓይነት መልኩ ከጥቅሙ ይልቅ ኪሳራው በሚያመዝነው አጀንዳ ላይ ገብተን የታራክ ተወቃሾች ከመሆን ለመትረፍ ራሳችንን ማንኛውም ዓይነት ድጋፍ ከመስጠት በመቆጠብ ዜግነታዊ ግዴታችንን እንወጣ ዘንድ ጥሬን አቀርባለሁ።

ሀገር ነጻ ስትወጣ በግርግር ሳይሆን በሥራ የሀገራችን እና የሕዝባችን ታሪክ እንለውጣለን!!
ዲ/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል

Wednesday, April 27, 2011

የምድሪቱ ጉዞና የማንቂያው ደወል ድምፅ(dejesemay)

የምድሪቱ  ጉዞና የማንቂያው ደወል ድምፅ
(ጌዲዮን)
 "ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላዕክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም "(ማቴ 24፡ 36)
" በመሸ ጊዜ ሰማይ ቀልቷልና ብራ ይሆናል ትላላችሁ፡፡የሰማዩን ፊትማ መለየት ታውቃላችሁ የዘመኑንስ ምልክት መለየት አትችሉምን?" (ማቴ 16፡3)
"ምሳሌዋንም ከበለስ ተማሩ ጫፏ ሲለሰልስ ቅጠሏም ሲያቆጠቁጥ ያን ጊዜም በጋ እንደቀረበ ታውቃላችሁ፡፡" (ማቴ 24፣32)
የዘመንን ፊት ስለመለየት ወይም "ስለዚያች ቀንና ሰለዚያች ሰዓት" ሰለተባለው ድንገተኛ ክስተት ለማወቅ የተለየ ወርክ ሾፕ እና ሲምፖዚየም ማዘጋጀት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ቤተ ሙከራ ማካሄድ በብዙ ሚሊዮን ሰልፈኛ አደራጅቶ በአደባባይ አመፅ መቀስቀስ አልፎም የአርባ ቀን ጾም ፀሎት መያዝ ላይጠበቅብን ይችላል፡፡ የዘመኑን ፊት ማን እንዲህ በቀላሉ ይለያል? የሚገርመው ትውልድ እንዲህ በሰለጠነበት እና ዘመን እንዲህ በረቀቀበት የመሬታችን ጉዞ ውስጥ ለአንድ ጊዜ የሚሆን የሰው ልጅ ከተነገረላት በለስ ተምሮ የበጋን መቅረብ ከመገመትና ከመተንበይ ባለፈ ለበጋና ለክረምት መፈራረቅ ከመሬት ዑደትና ከተፈጥሮ ክስተት በቀር እግዚአብሔር ስለሚባለው የነገሮች ሁሉ መጀመሪያና መጨረሻ የክስተቶች ሁሉ ማጠንጠኛ ማሰብ ቆም ብሎም መጠየቅ አይፈልግም፡፡ ያመዋል ምን አልባትም ይህን የማድረግ የህይወት አቅጣጫው አሁን ካለበት ሁኔታ 360 ዲግሪ ዞሮ ህይወትን ሌላኛዋ መልክ እንዲያጠና ስለሚገደድ ይፈራል፡፡ የሚፈልገው በደመ ነፍስ መኖር ነው፡፡ በመብላት በመጠጣት ልዮ ፋሽን በማሳደድ ቪላ በመገንባት ቆንጆ ሴቶች (ወንዶች) በመምረጥ የተሻለ የስራ ቦታ በማመቻቸት ተሰሚነት በሚያስገኙ መድረኮች አስገራሚ ዲስኩሮችን በማሰማትና ምድሪቱን በአሸናፊነትና በለውጥ ማማ ላይ ማስቀመጥ ነው፡፡
እኛ እኮ ጉዶች ነን፡፡ እጅግ የበዛን የበዛብን ጉዶች ሁሌም የህይወትን አንድ መልክ ብቻ የምንመዝን፡፡ ለሰው ለትውልድ ለህዝብ ለም ዲሞክራሲን ስንሰጥ ዲሞክራሲን  ስንሰብክ በራሳችን ላይ የጨከንን አምባገነኖች ነን፡፡ ነፍሳችን በነፃነት እንዳታስብ ህሊናችን የሚያምንበትን እንዳናራምድ እውነትን በእውቀት የገደልን እና መልስ ለሚሹ የውስጥ ጩህትና ኡኡታችን የበዛን የበዛብን ቢሮክራቶች  እና እንዴት ለራሳችን ዴሞክራሲን እንስበክ ? ይልቁኑ "ይህ ልጃችን እንደሆነ እውርም ሆኖ እንደተወለደ እናውቃለን፡፡ዳሩ ግን አሁን እንዴት እንዳየ አናውቅም ወይንም ዓይኖቹን ማን እንደከፈተ እኛ አናውቅም ጠየቁት እርሱ ሙሉ ሰው ነው እርሱ ስለራሱ ይናገራል " ማለት ይቀለናል ቀላሉ የማምለጫ መንገድ ይሔ ነንውና ታዲያ ለነፍሳችን ምን ዲሞክራሲ ያስፈልጋታል? ምክንያቱም
"አይሁድን ስለፈሩ ይህን አሉ" ለምን ይህን አሉ? እነሱ ከዘመኑ ፊት ይልቅ ፍርሃታቸው የሰው ፊት ነበርና ይህን አሉ፡፡ ይህን በማለትም ማህበራዊ ኑሮን እድርና እቁብን ሰርግ መልስ ቅልቅልን ገናና ፋሲካን በፍቅር በህብር በፌሽታ ያሳልፋሉ፡፡ ይህ ባይሆን ደግሞ "እርሱ ክርስቶስ ነው ብሎ የሚመሰክር ቢኖር ከምኩራብ እንዲያወጡት አይሁድ ከዚህ በፊት ተስማምተው ነበርና" (ዮሐ 9፡18-23) ስለተባለ የክህደት አድማ በአዋጅ ተለፈፈ፡፡ ሰው ለነፃነትና ለዲሞክራሲ አደባባይ ይወጣል  ድምፁን ያሰማል እዚህ በተቃራኒው መንፈሳዊ ዲሞክራሲን መንፈሳዊ አርነትን ለመግደል ለክህደትና ለእውነት ሞትና ስቃይን ለመጋበዝ ትውልድ ባንድ ተስማምቶ ሰልፍ ይወጣል ፡፡ ታዲያ ይህ ወገን የሰማይን ፊት እንጂ የዘመኑን ፊት እንዴት ይለያል? የዘመኑን ፊት በጽድቅ  በንጽህና በታማኝነት በትጋት በእውቀት በጭምትነት ራስን በመግዛት ለህሊና በመታመን ለእውነት በመኖርና በመሞት ከሁሉ በላይ ደግሞ በእምነት በመኖር የሚገኝ ነው፡፡ የሚገለጥ ነው፡፡ አሁን ማን ይሙት(እንበልና እንደተራቾቻችን) የዚህን ዘመን ፈተናና ስቃይ  ልብ ብሎ ለሚመረምር "ያን ጊዜ በጋ እንደቀረበ ታውቃላችሁ" እንደተባለላት በለስ  ጌታችሁ በደጅ እንደቀረበ እወቁ፡፡ ማለትም ከግንዛቤ ማስወጣት ይኖርብን ይሆን ወይስ "ስምንተኛው ሺ ቀርቧል" እየተባለ የፌዝ ማጣፈጫ የሆነው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ምጻአት ለኛ ከቁም ነገር የሚጻፍ አልሆነብን ይሆን ? እኔ ግን የምድሪቷ ጉዞና የደውል ድምጽ በለሆሳስ እያስተጋባ እንደሆነ አስባለሁ፡፡ የሚያስደነግጠኝ ግን ነገሩ ሁሉ ልክ እንደ ኖህ እንደ ሎጥ ዘመን ታሪክ "የአስረሽ ምችው ዘመን ታሪክ" አንዳይደግም ነው፡፡               
"ሊበሉ ሊጠጡ ተቀመጡ ሊዘፈኑ ተነሱ" አይነት
ፍቅር ሲቀዘቅዝ፣ ወንድም ወንድሙን ሊያጠፋ ሲነሳ ስጋ ሁሉ ለራሱ ነፍስ ብቻ ሲጠበብና ሲጨነቅ፣ ወላጅ በአደባባይ ሲዋረድ፣ የቤተክርስቲያን ክብር በስጋዊያንና በአለማውያን ልክ የለሽ ምኞት ሲገሰስ፣ ጽድቅ፣ ቅድስና፣ ቅንነት፣ ታማኝነት፣ ራስን መግዛት፣ በጎነትና ንፁህ አምልኮ . . . . የሞኞች ስብከት ሆነው ሲተረኩ እንዴትስ የዘመኑ መልክ ለትውልዱ ጠፍቶታል፡፡ ለማለት እንገደድ ይሆን? ጭንቁ የሚጀምረውም እዚህ ላይ ነው፡፡ አልያም ደግሞ ግድ ከሆነብን እንደ ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሀን ወቅታዊ ክስተቶችን እየተከታተልን ለምዕመኖቻችን ማሳወቅ ግድ ሊለን ነው፡፡ ዕምነት ያልከፈተው አይን ጋዜጣና፣ ቴሌቭዥን ወይም የቴክኖሎጂው "በረከት" የዲሽ አገልግሎት በምድራችንና በዘመናችን መካከል ላይ የሚፈፀመውን ጉድ እቤታችን ድረስ ስበው ስለሚያመጡልን "ወይ ጉድ" እያልን እየተደመምን እጃችንን በአፋችን ላይ እያኖርን ቀኖቻችንን እንገፋለን፡፡ ንቁና ብልህ የዕምነት ሰው ግን ከመጽሐፍም ከዘመንም እየተማረ ለእግዚአብሔር እውነት ይገዛል፡፡ አሁንም ንቁና ብልህ ሰው ከዘመኑ ፊት እየተማረ ከዓለም ጋር ያለውን ቁርኝት አቋርጦ ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ጽኑ ህብረት ይበልጡኑ ያጠናክራል፡፡
ü ህዝብ በህዝብ ላይ ሲነሳ እያየን
ü የምድር መናወጥ የሬክታር መጠኑን እየለካን
ü ጎርፍና የነፋስ ጉልበትን እየመዘንን
ü የፍቅር መቀዝቀዝና የጥላቻ መጠንን መበርከቱን እየቃኘን
ü ጦርነትን ጦርንና የጦር ወሬን እያደመጥን
"ወይ ስምንተኛው ሺህ" እያልን እየተረትን እምናልፍ ከሆነ በዕርግጥም የእውነት መስመሩን ስተናልና ቆም ብለን እናስብ ለኛ የሚገርመን
ü የመካከለኛው ምስራቅ ነውጥና የህዝቦች አለመረጋጋት ነወይ?
ü የግብፅ ብጥብጥና የሆስኒ ሙባረክ ከስልጣን መልቀቅ ነወይ?
ü የሊቢያ ፈተናና የሙዐመድ ጋዳፊ ጭካኔ ነወይ?
ü የሱማሊያ መበታተንና የባህር ላይ ውንብድና ነወይ?
ü የሆሳማ ቢንላደን አመፅና የመስከረሙ 1 የአሜሪካ ህንፃ መጋየት ነው ወይ?
ü ወይንስ የሶቪየት ህብረት መበታተን የዩጎዝላቪያ መለያየት  የአይቮሪኮስታውያን አመጽ?
እኛ እኮ አውራቂስንም እናውቃለን ኖህና የሎጥ ታሪክንም እናውቃለን የእስራኤልና የፍልስጤምንም ሆነ የሮማውያንን ወረራ ከመፅሃፍ ተምረናል በምልክት የምንደነግጥና የምንቦርቅ ሳንሆን በተከፈቱ የዕምነት አይኖች የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ዳግም ምፅዐት በእምነትና በተስፋ የምንጠባበቅ ነን፡፡ ስለዚህ የጌታ ምፅዐት የሚያስደነግጠን ሳይሆን በፍቅር የምንጠብቀው ነው የሚሆነው ለዚህ ደግሞ ዝግጁ እንድንሆን መፅሃፍ እንዲህ ይለናል ፡፡
 "ያን ግን እወቁ ባለቤት ከሌሊቱ በየትኛው ክፍል ሌባ እንዲመጣ ቢያውቅ ኖሮ በነቃ ቤቱም ሊቆፈር ባልተወም ነበር፡፡ ስለዚህ እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ የሰው ልጅ በማይታሰብበት ሰዓት ይመጣልና ፡፡" (ማቴ 24 ፡43)
ይመጣልና በእግዚአብሔር ግንዛቤና እውቀት " ይመጣል " ነው አንዳችም ክፍተት አንዳችም ጥርጣሬ አንዳችም የምናልባታዊነት ድምፀት  የለውም፡፡ ጌታችን ኢየሱስ የምድርን ጫፍ ከዳር እስከዳር ሊረግጥ ያለአንዳች ጥርጥር በዘመኑ ፍፃሜ ወደእኛ ያመጣዋል፡፡የምድሪቱ ፍፃሜን የሚያበስረው የደውል ድምፅ ከትላንት ይልቅ ዛሬ ከዛሬም በላቀ ሁኔታ ነገና ከነገ በስቲያ በምድራችን በጉልህ መደመጡ የማይቀር እውነት ነው፡፡እና ጥንቃቄን ለእናንተ እናስታውሳለን፡፡ ትጋትን ለናንተ " እርስ በእርስ ተመካከሩ " በተባለው መንፈስ ውስጥ ሆነን እንመክራለን፡፡ የእግዚአብሔርን ቃል በጥንቃቄ በመመርመር ከቃሉ ውስጥ በሚገኝ የዘመኑን ፊት የመለየት ጥበብ ተክነን ከእግዚአብሔር ጋር ያልተቋረጠ ህብረትን  እንመሰርታለን፡፡ በምድር የምንኖረው የእርሱ እውነተኛ ወኪሎች ሆነን ነውና ውክልናችንን በትክክለኛው የተልዕኮ ፈፃሚነታችን  መስመር አስይዘን የምድር ጉዞአችንን ልናጠናቅቅ ተስፋ እናደርጋለን እናምናለንም ፡፡ የማንቂያው የደውል ድምፅ የሚነግረን ልዩ መልዕክት ቢኖር በትጋትና በዝግጁነት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን መመለስ እንድንጠብቅ ነው፡፡ 

Monday, April 25, 2011

በጎውን ማን ያሳየናል የሚሉ ብዙ ናቸው== dejesemay

‹‹በጎውን ማን ያሳየናል የሚሉ
ብዙ ናቸው››
              (መዝ. 4፥6)፡፡
 
ስለ ዘመናችን ድንቅነት ብዙ ተነግሯል፡፡ የንግግሩ ምራቅ ሳይደርቅ ግን አሳዛኝነቱ ይተረካል፡፡ ዘመናችን ከተደነቀባቸው ነገሮች አንዱ የመረጃ ዘመን መሆኑ ነው፡፡ ሰዎች ስለ ራሳቸው ሳይሆን ስለ ሌሎች፣ ስለ ጎረቤታቸው ሳይሆን ስለ መካከለኛው ምሥራቅ ብዙ መረጃዎችን የሚሰሙበት ዘመን ነው፡፡ የመስማት አንዱ ዓላማ ለመመካከር፣ መራራው ወደ ጣፋጭ እንዲለወጥ ለመጸለይ ነው፡፡ የመረጃው ዘመን ግን ሰምቶ ማዳነቅ ብቻ ነው፡፡ ችግሮች ብዙ ናቸው፣ የመፍትሔ ድምፆች ግን አይሰሙም፡፡ ብዙ የመረጃ መረቦች የጭንቅ ወሬ ካጡ ይጨነቃሉ፡፡ የጦርነት፣ የተፈጥሮ አደጋ፣ የእርስ በርስ መተላለቅ ትልቅ ርእሳቸው ነው፡፡ በአገራችን በኢትዮጵያ በ1998 ዓ.ም በነበረው ግርግር አንድ የጋዜጣ አዘጋጅ ለጓደኛው ሲናገር፡- ‹‹ይህ ግርግር ሳይበርድ ለሦስት ወር ከቀጠለ የጀመርኩትን ቤት እጨርሳለሁ›› እንዳለ፣ ጭንቅ ባላለቀ እያሉ የሚሳሉ፣ እንደ ዕድር ጡሩንባ ነፊ ሞተ እንጂ ተነሣ የማይሉ፣ እንደ ጠመንጃ አፈ - ሙዝ ከአፋቸው ደህና የማይወጣ፣ ያልተባረኩ አንደበቶች በዝተዋል፡፡ ብዙ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን እንለዋውጣለን፡፡ ሁሉም የሚያመነዥጉት ያንን ክፉ ነው፡፡ አዋቂዎቹ የሚሰጡት ትንታኔ የሚመጣውን ቀውስ ጠቋሚ ነው፡፡ ስለዚህ የግለሰቦች ቀውስ እያለፈ ዓለም ራሷ እየቀወሰች መሆኗን እንረዳለን፡፡ ግለሰቦች ሲቃወሱ ምድር ችላቸው ብዙ ዘመን ኖረናል፡፡ ምድር ከቀወሰች ግን ማን ይችላታል@
ተበልቶ እንዳለቀ አጥንት ወይም የበቆሎ ቆረቆንዳ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችን ብናገላብጣቸው ለጥጋብ የሚሆን አንድም ነገር የለባቸውም፡፡ ወደ ኢንተርኔት ጫካም ስንገባ ወሬ ከመንግሥታዊ ተቋማት ወደ ግለሰብ ተቋማት ዝቅ ብሎ፣ ‹‹ሐሜት ድሮ ቀረ በቃል ብቻ›› የሚሉ የጽሑፍ ሐሜተኞችን እናገኛለን፡፡ የሰውን ስም ቡና ላይ ከማንሣት ድረ - ገጽ ላይ ወደ ማንሣት ተሸጋግረናል፡፡ ብሔራዊ የነበረውን ኃጢአታችንን ዓለም አቀፋዊ አድርገነዋል፡፡ ጫካ ገብቶ በጥይት የመዋጋት ዘመን በኢንተርኔት ውስጥ መሽጎ በስም ማጥፋት አረር እንደ ተለወጠ እያየን ነው፡፡
ጉድ ያለበት የሰው ልጅ የሌላውን ጉድ ለማውራት በጀት የባጀተበት ዘመን መሆኑን እናያለን፡፡ ዘመኑና ሥልጣኔው መስተዋት ሳይሆን መነጽር መሆናቸውን እናስተውላለን፡፡ መስተዋት ራስን ያሳያል፣ መነጽር ሌላውን ያሳያል፡፡ በክፉ ወሬዎች በተከበበው ዘመን የብዙዎች ነፍስ ተጨንቃለች፡፡ በሩቅ ስላለው ሰው እያወቁ ራስን አለማወቅ፣ የሌሎችን ክፋት እየተረኩ የእግዚአብሔርን በጎነት መዘንጋት ለሰዎች ዕረፍትን አልሰጣቸውም፡፡ በእውነት፡- ‹‹በጎውን ማን ያሳየናል@ የሚሉ ብዙዎች ናቸው›› (መዝ 4፥6)፡፡
ስለ ሰዎች ክፋት አንድ ሰዓት ማውራት መቻል ስለ እግዚአብሔር በጎነት ዐሥር ደቂቃ መነጋገር አለ መቻል በጣም ያሳዝናል፡፡ የሰው ልጅ የትኛውም ማንነቱ አያሳርፍም፡፡ እንኳን ከድካሙ ከብርታቱም ጉድለት አለበት፡፡ ነቢዩ፡- ‹‹ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው›› ያለው ለዚህ ነው (ኢሳ. 64.6)፡፡ የሚያሳርፈው የመስቀሉ ሥራ ብቻ ነው፡፡ ስለ ክፉ አንድ መጽሐፍ መጻፍ ስለ መጽናናት ግን አንድ መስመር አለመጻፍ በእውነት ምስኪንነት፣ የሞትም አገልጋይ መሆን ነው፡፡ የሰዎችን መልካምነት በካባ እየሸፈኑ ትንሽ ስህተታቸውን በአጉሊ መነጽር ማየት በእውነት አለመታደል ነው፡፡ ዘመናዊነትን ስናየው የክፋት ማፍጠኛ እንጂ የመልካም ነገር ማፍጠኛ አለመሆኑ ያሳዝናል፡፡
ብዙ የዓለማችን ሕዝቦች ከመረጃ መረቦች ራሳቸውን እያገለሉ ነው፡፡ የራሳቸውን ችግር ሳይፈቱ ስለ ሰው ኃጢአት መነጋገር እየሰለቹ ነው፡፡ ልክ ያልሆኑ ነገሮችን ከሚያሰሙ ስብከቶች ልክ የሆነውን ወደሚያሳዩ አገልጋዮች ዘወር እያሉ ነው፡፡ የሰው አእምሮ በብዙ ጭንቀቶች በተወጠረበት በዚህ ዘመን፣ ብዙ አደንዛዥ ዕፆች በሚወሰዱበት በዛሬው ጊዜ የሚበጀው ሰላማዊ መልእክት ብቻ ነው፡፡ በራሳቸው መወደድ ያልቻሉ ሌላውን እያስጠሉ ለመወደድ የሚሹ ሰዎችን ብዙዎች እየራቁ ‹‹በጎውን ማን ያሳየናል@›› እያሉ ነው፡፡ እኔ ቆንጆ ነኝ ለማለት እገሌ አስቀያሚ ነው ማለት አስፈላጊ እንዳልሆነ ሕዝባችን እያስተዋለ ነው፡፡ እናንተን የምንቀበላችሁ በራሳችሁ ልክ ስትሆኑ እንጂ እነ እገሌ ስለ ተሳሳቱ አይደለም እያለ ነው፡፡ በእውነት ጠብን ሳይሆን ፍቅርን የሚዘሩ፣ ክርክርን ሳይሆን መግባባትን የሚያመጡ አገልጋዮች እየተፈለጉ ነው፡፡ 
ራሳችንን ስናየው ሬዲዮን በደንብ ሳንጠቀም ቴሌቪዥን የጀመርን፣ ታይፕን በደንብ ሳንጠቀም ኮምፒዩተርን የተከልን፣ አጠገባችን ካለው ሰው ጋር ሳንግባባ ዓለም አቀፍ መረጃ ውስጥ አሳብ የምንሰጥ፣ ከወንድማችን እየተጣላን ከዓለም አቀፍ ወጣቶች ጋር ማኅበርተኛ መሆን የምንፈልግ፣ በጾም ከበሮ መምታትን እየጠላን ወገናችንን በስድብ የምንደልቅ፣ ያጎረስነው ሰው እያነቀ በላይ በላዩ የምናጎርስ፣ ከሥልጣኔው ክፉውን የምንጠቀም ነን፡፡
በብዙ ውጣ ውረድ ያለፈው ሕዝባችን ዕረፍትን ፍለጋ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲመጣ በሁከት ድምፅ እያሸበርነው፣ ማንንም አትመን እያልን አውሬን እየሳልንለት፣ የሥጋ ቅንዓታችንን ሃይማኖታዊ ካባ አልብሰን እያስጨነቅነው ነው፡፡ ወጣትነቱን በትክክለኛ ጎዳና ለመምራት የመጣውን ወጣት ሃይማኖታዊ ጠብ እንዲጣላ፣ በዝማሬ በስብከት ካጽናኑት አገልጋዮች ጋር እንዲታኮስ እያደረግነው ነው፡፡ ከዓለም ሁከትን ሸሽቶ የመጣው ትውልድ፣ በቤተ ክርስቲያን የሁከትን ድምፅ ሲሰማ ‹‹በጎውን ማን ያሳየናል@›› እያለ እየተጨነቀ ነው፡፡ ያሉት አገልጋዮች ተቀንሰው አይደለም፣ በእጥፍ ተጨምረው እንኳ ሕዝቡን መድረስ አይቻልም፡፡ ከዚሁም ላይ ስም እየሰጠን እየቀነስን ቤተ ክርስቲያንን የወላድ መሐን ማድረጋችን፣ የመናፍቃኑን አዳራሽ አለመሙላት ከውስጥ መግፋታችን አሳዛኝ ነው፡፡ ብዙ የሳጥናኤል የውስጥ ካድሬዎች ከውስጥ ሆነው ሲገፉ ከደጅ ያሉት ደግሞ ይቀበላሉ፡፡ በዋጋ የተሰበሰበውን ሕዝብ ያለ ዋጋ መበተን፣ ፍቅር አጥቶ ከዓለም የመጣውን ሕዝብ ጠብና ክርክር ማስጠናት ተገቢ አይደለም፡፡ አንድ ሕገ መንግሥት (መጽሐፍ ቅዱስ) ይዘን መለያየት ለአረማውያን ሰይፍ ራሳችንን ማዘጋጀት ነው፡፡
ሕዝባችን የፍቅር ሰባኪዎች ሲፋቀሩ፣ የይቅርታ አዋጅ ነጋሪዎች ይቅር ሲባባሉ ማየት ይፈልጋል፡፡ የቃል ስብከታችንን ከተማው ጠግቦት በሕይወታችን ስንኖረው ማየት እየፈለገ ነው፡፡ በየአድባራቱ እየታየ ያለው የጠብ አዝመራ፣ ጭር ሲል የማይወዱት የጠብ ጫሪዎች፣ በሰው ሬሳ ለመኖር የሚያቅዱ የክርስቶስ ጠላቶች፣ ስሜታቸውን መግዛት ያቃታቸው የገምቦኞች ክተት ነው፡፡ ሕዝባችን የእግዚአብሔርን ቃል ዳኛ አድርጎ ማነው የሳተው? ማለት አለበት፡፡ ጋዜጣ ላይ የወጣ ሁሉ የመጨረሻው እውነት ሆኖ ሊታየው፣ በኢንተርኔት የተለቀቀ ሐሜት የሲኖዶስ ውሳኔ አድርጎ ሊቀበለው አይገባም፡፡ ሁሉን የሚበክሉ ሚዛን የለሾች፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ከመልካም አገልጋዮች ብቻ ሳይሆን ከተሰቀለው ጌታ ሊለዩአት የተነሡ፣ ወንጌልን ከኦሪት፣ ክርስቶስን ከሙሴ፣ መጽሐፍን ከተረት መለየት ያልቻሉ፣ እውነት በሚመሰል ሐሰት፣ ቅንዓተ ቤተ ክርስቲያን በሚመስል ራስን መስበክ ሕዝቡን እያደናገሩት ይገኛሉ፡፡ ሕዝቡም የሚይዘውን የሚጨብጠውን አጥቶ ‹‹በጎውን ማን ያሳየናል@›› ይላል፡፡
ወገናችን ዕድሜውን በሙሉ ብዙ ጭንቆችን ያየ፣ ብዙ ጦርነቶችን ያሳለፈ፣ የኑሮ ጠባሳ መልኩን ያጠፋው፣ በብዙ ቀBስለትም የሚያቃስት ነው፡፡ በዚህች አገር ላይ የኖረ፣ ያለፉትን ዘመናት ሰቆቃ ያየ ወገን፣ ሕዝቡን እንደ ገና አያስጨንቅም፡፡ የሚያጽናናውን ወንጌል በመስበክ ያረጋጋ ነበር፡፡ ጭጋግና ደመናው ነገን አላሳይ ላለው ወገን፣ ዝናብ የሌላቸው ደመናዎች ላደከሙት ሕዝብ የወንጌልን ማዕድ የምናቀርብበት ዘመን አሁን ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን መወከል የማይችሉ አጽራረ ወንጌሎች የአዋቂዎችን ልብ እየሰበሩት፣ ትውልዱ ያዳነውን ጌታ እንዳያይ የክርስቶስን ደም እያክፋፉበት መሆኑ ያሳዝናል፡፡ መሳሳት የማይደክማቸው፣ ከትላንት ጥፋት የማይማሩ በመሆናቸው ሊለቀስላቸው ይገባል፡፡ ሊሰበክ ሊታወቅ የሚገባው ማን ነው@ የቤተ ክርስቲያን መሠረትና ጉልላትስ ማን ነው? ኢየሱስ ክርስቶስ አይደለምን? ‹‹ሞኝ ባያፍር ዘመዱ ያፍራል›› እንዲሉ በእነዚህ ሰዎች እስከ መቼ እናፍራለን? በአይሁድ ምኩራብ ክርስቶስ በተስፋ ይሰበካል፣ አይታፈርበትም፡፡ በእስላም መስጊድ ዒሳ ተብሎ ይነሣል፡፡ በእነዚህ ሰዎች ዘንድ ግን ኢየሱስ ክርስቶስን የጠራ በውግረት ይሙት ተብሎ ይፈረድበታል፡፡ ጠላትነታቸው ከፍጡር ሳይሆን ከተሰቀለው ጌታ ጋር ነውና ንስሐ እንዲገቡ እንጋብዛለን፡፡ ነፍሳቸውም በሐዋርያት ውግዘት ውስጥ ነች፡- ‹‹ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን›› (1ቆሮ. 16.22) በተባለው ቃል የታሠሩ ናቸው፡፡ 
ሕዝቡ በዕንባ የሚዘምረውን ዝማሬ ያንተ አይደለም ይሉታል፣ የራሱ ያልሆነ ነገር እንዴት ያስለቅሰዋል? ልቡን ያሳረፉለትን ሰባኪዎች መናፍቃን ናቸው ይሉታል፣ የተፈወሰበትን መጻሕፍት የባዕድ ናቸው ይሉታል፡፡ በዚህ ሁሉ ውስጥ ‹በጎውን ማን ያሳየናል? የሚሉ ብዙ ናቸው›› (መዝ 4፥6)፡፡
ሕዝባችንም አደባባዩን የያዙ እውነተኞች ናቸው ብሎ ማሰብ የለበትም፡፡ ቅንዓት በዲግሪም አይለቅምና አዋቂዎች ነን በሚሉ ፈሪሳውያን ግራ ሊጋባ አይገባውም፡፡ እውነት ምንድነው? ብሎ ሊጠይቅ፣ ክርስቶስን የማይወድ የተረገመ መሆኑን ሊገነዘብ ይገባዋል፡፡ ትላንት ያስተማሩት አገልጋዮች ዛሬ ጦርነት ሲታወጅባቸው የአንዱን ቀን ማጽናናታቸውን እንኳ አስቦ ለምን@ ሊል ይገባዋል፡፡ ባለቤቱ፡- ‹‹እኔ ኦርቶዶክሳዊ ነኝ›› እያለ አይደለህም ማን ይለዋል? እነዚህስ ስም አጥፊዎች ይህንን እንዲያደርጉ ፈቃድ የሰጣቸውና የወከላቸው አካል ማን ነው@ ማለት አለበት፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን በመግለጥ ሁሉንም አገልጋዮች በቃሉ መመዘን ይገባል፡፡ አሊያ ያለፉት ዘመናት ስህተት ሳያንስ ሌላ ደም በእጃችን እንዳይገኝ መጠንቀቅ ይገባል፡፡

የማያስተውል ሕዝብ ይገለበጣል

<<የማያስተውል ሕዝብ ይገለበጣል>>

ሁላችንም እንደምናውቀው የመገልበጥ አደጋ እጅግ ትልቅ ጉዳት ያለው ነው፡፡ በዓለማችን ላይ በዚህ አደጋ ምክንያት ብዙ ጉዳቶችን አይተናል፡፡ በአገራችንም የወቅቱ አሳሳቢ ጉዳይ በተሽከርካሪ አማካይነት የሚደርሰው የግጭትና የመገልበጥ አደጋ ነው፡፡
ሕይወት ሲጠፋ፣ ንብረት ሲወድም፣ አካል ጉዳተኝነት ሲጨምር ማየትና መስማት የጆሮአችን ቀለብ ከሆነ ሰንብቷል፡፡ ይህ አደጋም የሚከሰተው ማስተዋል በጎደላቸው አሽከርካሪዎች ምክንያት መሆኑ ግልጽና የሚታወቅ ነው፡፡ በዚህ ምክንያት በአገራችን ተሽከርካሪን መጠቀም ትልቅ ሥጋት እየፈጠረ መሆኑ ይታወቃል፡፡ መንግሥትም ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት የተለያዩ እርምጃዎችን ቢወስድም የሕግ አንቀጾች ቢረቀቁም አደጋው ግን በቊጥር ይቀንስ እንጂ ሥጋቱ አልቀረም፡፡
የዚህ አደጋ ትልቁ መንስኤ የማያስተውሉ አሽከርካሪዎች መብዛታቸው ነው፡፡ እንግዲህ አለማስተዋል ለመገልበጥ አደጋ ይዳርጋል፡፡ መፍትሔውም ማስተዋል ብቻ ነው፡፡ ውድ ሕይወትን እንዲሁም ዋጋ ያለው ንብረትን ለከፋ አደጋ ላለመዳረግ ማስዋል ትልቁ ቁልፍ ነው፡፡
ነቢዩ ‹‹የማያስተውል ሕዝብ ይገለበጣል›› በማለት ይናገራል፡፡ ለካስ ወገኖች! በመንፈሳዊውም ዓለም ትልቅ የመገልበጥ አደጋ አለ፡፡ ይህ አደጋም የሚከሰተው እንዲሁ ባለማስተዋል ነው፡፡ ነቢዩ ይህንን በተናገረበት ምዕራፍ ላይ የእስራኤል ሕዝብ ስለነበረበት መንፈሳዊ ውድቀት አስቀድሞ በመግለጥ ነው፡፡ ምዕራፉ ሲጀምር እንዲህ ይላል፡ - ‹‹ እናንተ የእስራኤል ልጆች ሆይ፡- እውነትና ምሕረት እግዚአብሔርን ማወቅ በምድር ስለሌለ እግዚአብሔር በምድር ላይ ከሚኖሩ ጋር ክርክር አለው፡፡›› (ሆሴ. 1÷ 1)
ለዚያ ሕዝብ መገልበጥ ምክንያት እውነትና ምሕረት እግዚአብሔርም ማወቅ አለመኖሩ ነው፡፡ ከእውነት ይልቅ ለሐሰትና ለስህተት ከምሕረት ይልቅ ለፍርድና ለነቀፋ እግዚአብሔርን ከማወቅ ይልቅ ስለሰዎች ለማወቅ የሚኖር ሕዝብ ትልቅ የመገልበጥ አደጋ እንደሚደርስበት ቃሉ ያረጋግጣል፡፡ የክርስትናው መሠረት እውነትና ምሕረት እንዲሁም እግዚአብሔርን ማወቅ ነው፡፡
እውነት፡ - የአምልኮ መሠረት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ 4 ÷ 24 ላይ እንደተናገረው እግዚአብሔርን ማምለክ በእውነትና በመንፈስ ነው፡፡ ሕዝብንም አርነት የሚያወጣው እውነት ነው፡፡ ቃሉም ‹‹እውነት አርነት ያወጣችኋል›› (ዮሐ. 8÷32) ይላል፡፡ እግዚአብሔርን በልማድ፣ በሥርዓትና በስሜት ለማምለክ የምናስብ ከሆነ ክርክራችን ከእግዚአብሔር ነው፡፡ ልማዳችንም ሆነ ሥርዓታችን ፋይዳ የሚኖረው አምልኮአችን እውነት ላይ ሲመሠረት ነው፡፡ ያለበለዚያ በአሸዋ ላይ እንደተመሠረተው ቤት የወሬ ንፋስና የመከራ ወጀብ በመጣ ጊዜ ቤቱ አደጋ ላይ መውደቁ አይቀርም፡፡
ምሕረት፡- ከእግዚአብሔር ባሕርይ አንዱ ምሕረት ነው፡፡ ይህም እግዚአብሔር ለእኛ ያለው መልካምነት ነው፡፡ መጽሐፉ እንደሚነግረን እርሱ ለክፉዎችና ለመልካሞች ፀሐይንና ዝናብን ያለ ልዩነት ይሰጣል፡፡ እኛ ብንሆን ግን ለጠላነውና ለወደድነው በፈረቃ እናከፋፍል ነበር፡፡ ከእርሱ የምንማረው ግን ለምንጠላቸው እንኳ መልካምነት እንደሚገባ ነው፡፡ በዚህ ዘመን ግን የሚወዱንን እንኳ መውደድ እያቃተን ነው፡፡
እግዚአብሔርን ማወቅ፡- እግዚአብሔርን ማወቅ የክርስትናው ዐቢይ ነገር ነው፡፡ የማናውቀውን አምላክ እንዴት ልናመልክ እንችላለን? ብዙዎች ግን ሳያውቁት ያመልኩታል፡፡ ጳውሎስ በአቴና ሳለ የአቴና ሰዎች ሳያውቁት መሠዊያ ሠርተው የሚያመልኩት አምላክ እንደነበራቸው አየና የማያውቁትን አምላክ ማምለክ ተገቢ እንዳልሆነ በመግለጽ ብቸኛውን አምላክ አስተዋወቃቸው፡፡ ዛሬም ብዙዎች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አያውቁትም ግን በስሙ ይጠራሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያንን አያውቋትም ግን ስለእርሷ ይሟገታሉ፡፡ እውነተኛ ክርስቲያኖች ለመሆናቸውም የሕይወት ምስክርነት የሌላቸው ናቸው፡፡ ወገኖቼ! ይህ ቃል እኛን ኦርቶዶክሳውያንን ይመለከታል፡፡ የአብዛኛው ሕዝባችን መንፈሳዊ ሕይወት በእነዚህ መሠረቶች ላይ የቆመ አይደለም፡፡ ሆሳዕና! ብሎ ለማመስገን የሚቸኩል ዳግመኛም ስቀለው! ለማለት የማይዘገይ እንደ ውሃ በቀደዱለት ቦይ የሚፈስ ነው፡፡ ነገር ግን ወገኖቼ! ለማመስገንም ለመርገምም አንቸኩል፡፡ የምንሰማውንና የምናየውን በማስተዋል እንመርምር፡፡ ቃሉ ‹‹የማያስተውል ሕዝብ ይገለበጣል›› ይላልና፡፡
የእስራኤል ሕዝብ የተነቀፈው መሠረታዊ የእምነት መገለጫውን በማጣቱ ነው፡፡ ያለ እውነት ልናመልክ አንችልም፡፡ ያለ ምሕረት (በጎነት) ምስክርነት የለንም፡፡ እግዚአብሔርን ሳናውቀውም የእርሱ ነን ማለት አንችልም፡፡ ይህ ከሌለን ክርክራችን ከሰው ሳይሆን ከራሱ ከእግዚአብሔር ጋር ነው፡፡ ቃሉም ይህንን ያረጋግጥልናል፡፡ ‹‹እግዚአብሔር በምድር ላይ ከሚኖሩ ጋር ክርክር አለው፡፡›› (ሆሴ. 1÷ 1)
ብዙዎች ለሃይማኖት የሚከራከሩ እንጂ ለሃይማኖት የሚመሰክሩ አይደሉም፡፡ ምስክሮች ልንሆን መጠራታችንን ቃሉ ይናገራል፡፡ ምስክር ያየና የሰማ ነው፡፡ ስለማናውቀው እግዚአብሔር እንከራከራለን፤ ስለማናውቃት ቤተ ክርስቲያን እንሟገታለን፡፡ የእኛን ማመን የምንገልጠው ሌሎችን በመስደብና በመንቀፍ ነው፡፡ ለክርስትናችን አብነት የምናደርገው ማንን ይሆን? መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ከሆነ እስኪ የእርሱን ፈለግ እናስተውል እንኳን ሊሳደብ ሲሰድቡት ምላሽ አልሰጠም፡፡ እኛ ግን በአካል መሳደብ ባንችል በዘመናዊ የመገናኛ መንገድ ለመሳደብ በአደባባይ የተገለጥን ነን፡፡
በድረ-ገጻቸው የሰውን ስም እያብጠለጠሉና የስድብ ናዳ እያወረዱ በጽሑፋቸው መዝጊያ ላይ ቸር ወሬ ያሰማን¡¡¡  በማለት የሚቀልዱ የቤተ ክርስቲያኒቱ ተቆርቋሪዎችና የክርስቶስ ወገኖች መሆናቸውን ይናገሩ እንጂ ከእነርሱ የሚወጣው የስድብ ቃል ለጆሮ የሚቀፍና የመንደር ሰዎች እስኪመስሉ ድረስ ለሕዝቡ የስድብ ዓይነት ለማስተማር እንጂ በእውነት ከኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን የተማሩና ለአገልግሎት የተጠሩ አይመስሉም፡፡ ከዚህም ባሻገር ቤተ ክርስቲያንን በአንድ የሰንበት ት/ቤት ማደራጃና መምሪያ ሥር ባለ የጽዋ ማኅበር ለመምራት የሚያስቡ ተራራ ልብ ያላቸው ናቸው፡፡
ወገኖቼ! ከአንደበታችን የስድብና የጥላቻ እንዲሁም የሌሎችን ሕይወት የሚያብጠለጥል ቃል እያወጣን ቸር ወሬ ያሰማን¡¡¡  የሚል ምኞት ከኲርንችት በለስን ለመልቀም ከማለም የዘለቀ ልመና አይደለም፡፡ ቃሉም፡- ‹‹አትሳቱ እግዚአብሔር አይዘበትበትም፡፡ ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና›› (ገላ.6÷7) ይለናል፡፡ ከእኛ አንደበት መልካምና የበረከት ቃል ሳይወጣ ጆሮአችን መልካም ቃልን እንዲሰማ መመኘት መንፈሳዊ ቀልደኞች ያሰኘናል፡፡
ነቢዩ የሆሴዕን መጽሐፍ ምዕራፍ አራትን በሙሉ ስናነብ ላለንበት ዘመን በቂ መልዕክት ነው፡፡ የምዕራፉ አሳብ በሰፊው ቢተነተን መጽሐፍ የሚወጣው ነው፡፡ ነገር ግን ለዚህ ጽሑፍ የሚሆነንን ኃይለ-ቃል በቁጥር ስድስት ላይ ያለው ‹‹ሕዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቷል›› የሚለው ነው፡፡ ያ ሕዝብ እውቀት ያጣ ብቻ አልነበረም እውቀትንም የሚጠላ እንደነበረ ተገልጧል፡፡ ዛሬም ብዙዎች እውቀት ከማጣት የተነሳ ብቻ የጠፉ አይደሉም፡፡ እውቀትንም የሚጠሉ ናቸው፡፡ የዚህ መገለጫውን ከዛሬው አቋማችን እንገለበጥና ነገ ደግሞ ሌላ ሰዎች ሆነን መገኘታችን ነው፡፡ የመረቅነውን እንረግማለን፣ ያጸደቅነውን እንኮንናለን፡፡ ወገኖቼ! አይደክማችሁም? እስኪ ቆም ብላችሁ አስቡ ለመጣው ነገር ሁሉ ቤተ ሙከራ መሆን ይደክማል፡፡ የዚህ ችግሩ የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ማጣትና መጥላት ነው፡፡ ይሁን እንጂ ክርክራችን ከእግዚአብሔር ጋር በመሆኑ በምንፈርድበት ይፈርድብናል፤ በምንሰፍረውም ይሰፍርልናል፡፡ ‹‹የማያስተውል ሕዝብ ይገለበጣል››፡፡
በብዙዎቻችን ሕይወት እንደሚታየው ስለማንጠየቅባቸው ሰዎች ማንነት ስናጠና፣ ስንነቅፍ፣ ስንፈርድ የእኛን ተጠያቂነት እየዘነጋን መጥተናል፡፡ ነገር ግን ሁላችንም በክርስቶስ የፍርድ ዙፋን ፊት መቆማችን የማይቀር እውነት ነው፡፡ ሐማ መርዶክዮስን ለማሰቀል የአይሁድንም ሕዝብ ለማጥፋት ሲፈጥን በፍጻሜው ራሱን በመስቀል ላይ አገኘው፡፡ ዛሬም ብዙዎችን ከቤተ ክርስቲያን ስም በመስጠትና በማባረር  የሚተጉ ወደ መስቀላቸው ፍጻሜ እየፈጠኑ መሆናቸውን የረሱ ይመስላሉ፡፡ በየአዳራሹና በየዓውደ ምሕረቱ ሕዝብን እየጠሩና የሰዎችን ስም እያብጠለጠሉ የሌሎችንም አገልግሎት እየነቀፉ ሐማ እንደ መዘነው የጥፋት ገንዘብ  እነርሱም ገንዘብ በማሰባሰብ ሥራ የተጠመዱ ወደ ፍጻሜያቸው መቃረባቸውን ቢያውቁና ንስሓ ቢገቡ መልካም ነው፡፡ ዛሬም በንስሓ ለሚመለሱ ሁሉ አምላካችን የተዘረጉ እጆችና የተከፈቱ ደጆች አሉት፡፡ ይህንን ዕድል ፈንታቸውን ካልተጠቀሙበት ግን ቃሉ እንደሚል ‹‹እውነትን በአመፃ በሚከለክሉ ሰዎች በኃጢአተኝነታቸውና በአመፃቸው ሁሉ ላይ የእግዚአብሔር ቊጣ ከሰማይ ይገለጣልና›› (ሮሜ.1÷18)፡፡
ሕዝባችንም በየዐውደ ምሕረቱና የመሰብሰቢያ ቦታ ጥሪ ሲደረግለት የሚገኝ ይሁን እንጂ ለሚሰማው ቃል (ድምፅ) የሚያጣራበት ወንፊት የሌለው ነው፡፡ የእግዚአብሔር ሕዝብ ግን ‹‹መጽሐፍስ ምን አለ?›› በማለት የሰማውን ለመቀበልም ሆነ ለመጣል የእውነት ሚዛን ያለው ነው፡፡ ወገኖቼ! የእግዚአብሔር ቃል እውቀት ከሌለን የተባረከውን ሕዝብ ለመርገም እንደ በለዓም ስንቸኩል መንገዳችንም በፊቱ ጠማማ ሆኖ ከእግዚአብሔር ጋር እንዳንጣላ ልናስተውል ይገባል፡፡ ያለበለዚያ ‹‹የማያስተውል ሕዝብ ይገለበጣል!›› ተብሎ እንደተጻፈ የረገምነውን እንባርካለን!! እግዚአብሔር የባረከውን ሊረግም የሚችል የለምና፡፡
በመጨረሻ በሐዋርያው የቡራኬ ቃል ልሰናበት ‹‹ጌታ በነገር ሁሉ ማስተዋልን ይስጥህ›› (2ኛ ጢሞ. 2÷7)