Tuesday, February 15, 2011

ባሪያዎች ሊያረጉን (የገላትያ መልእክት ም 2፡6-14) ክ.3 ዲ. ተከስተ ጫኔ

የገላትያ መልእክት ም 2፡6-14

አለቆች የመሰሉት ግን በፊት ማን እንደነበሩ አይገደኝም እግዚአብሔር የሰውን ፊት አይቶ
አያዳላም አለቆች የመሰሉት አንዳች እንኳ አልጨመሩልኝምና (ቁ. 6)
በዚህ እርስ ውስጥ የጳውሎስን እና የዋና [የመጀመሪያዎችን] ሐዋርያት ስምምነት እና አንድነት
እንማራለን። ሙሉውን ቃል እንደሚከተለው ያንቡ፥
አለቆች የመሰሉት ግን፥ በፊት ማን እንደ ነበሩ አይገደኝም፤ እግዚአብሔር የሰውን ፊት አይቶ
አያደላም፤ አለቆች የመሰሉት አንዳች እንኳ አልጨመሩልኝምና፥ ተመልሰው ግን ጴጥሮስ ለተገረዙት
የሆነው ወንጌል አደራ እንደ ተሰጠው እንዲሁ ለእኔ ላልተገረዙት የሆነው ወንጌል አደራ እንደ ተሰጠኝ
አዩ፤ ለተገረዙት ሐዋርያ እንዲሆን ለጴጥሮስ የሠራለት፥ ለእኔ ደግሞ ለአሕዛብ ሐዋርያ እንድሆን
ሠርቶአልና። ደግሞ የተሰጠኝን ጸጋ አውቀው፥ አዕማድ መስለው የሚታዩ ያዕቆብና ኬፋ ዮሐንስም እኛ
ወደ አሕዛብ እነርሱም ወደ ተገረዙት ይሄዱ ዘንድ ለእኔና ለበርናባስ ቀኝ እጃቸውን ሰጡን፤ ድሆችን
እናስብ ዘንድ ብቻ ለመኑን፥ ይህንም ደግሞ ላደርግ ተጋሁ። ነገር ግን ኬፋ ወደ አንጾኪያ በመጣ ጊዜ ፊት
ለፊት ተቃወምሁት፥ ይፈረድበት ዘንድ ይገባ ነበርና። አንዳንድ ከያዕቆብ ዘንድ ሳይመጡ ከአሕዛብ ጋር
አብሮ ይበላ ነበርና፤ በመጡ ጊዜ ግን ከተገረዙት ወገን ያሉትን ፈርቶ ያፈገፍግ ነበርና ከእነርሱ ተለየ።
የቀሩትም አይሁድ ደግሞ፥ በርናባስ ስንኳ በግብዝነታቸው እስከ ተሳበ ድረስ፥ ከእርሱ ጋር አብረው
ግብዞች ሆኑ። ነገር ግን እንደ ወንጌል እውነት በቅንነት እንዳልሄዱ ባየሁ ጊዜ በሁሉ ፊት ኬፋን። አንተ
አይሁዳዊ ሳለህ በአይሁድ ኑሮ ያይደለ በአሕዛብ ኑሮ ብትኖር፥ አሕዛብ በአይሁድ ኑሮ ሊኖሩ እንዴት
ግድ አልሃቸው? አልሁት። (ገላ ፪፥ ፮ - ፲፬)
በዚህ ንባብ ውስጥ እውነት አለቅነትን እንኳ ያላግባብ ከሆነ የማታከብር መሆኗን እንረዳለን። አለቅነት
ከወንጌል እውነት ጋር ሲሆን ማዕረግ ነው። ከወንጌል እውነት ውጭ የሆነ አለቅነት ግን ሙስና ነው።
ሐዋርያው ጳውሎስ ዋነኞቹ ሐዋርያት ከጌታ ጋር በነበሩበት ዘመን አብሮ ባይኖርም አለቅነታቸውን
አልካደም ይህም በወንጌል እውነት ጸንተው በመገኘታቸው እንጂ ዝም ብለው አለቃ ስለሆኑ አይደለም።
የወንጌልን እውነት ባይዙ ኖሮ የነርሱ አለቅነት ለጳውሎስ ጉዳዩ አልነበረም። አለቆች በፊት ማን እንደነበሩ
አይገደኝም እግዚአብሔር የሰውን ፊት አይቶ አያዳላምና ይላል። ደግነቱ ግን ጳውሎስ ወደ ዋነኞቹ
ሐዋርያት ገብቶ የሚሰብከውን ወንጌል ባሳወቃቸው ጊዜ ምንም ስሕተት እንደሌለበት ማረጋገጣቸው
ነው። ሐዋርያው ጴጥሮስ፤ ሐዋርያው ዮሐንስ፤ ሐዋርያው ያዕቆብ አዕማድ መሆናቸውን ጳውሎስ
ተናግሯል። አዕማድ ማለት ምሰሶዎች ማለት ሲሆን በዚህ ክፍል ውስጥ ዋነኛ አለቆች ለማለት ነው።
ጌታ ወደ ቅዱሱ ተራራ ይዞ ወጥቶ በርሃነ መለኮቱን ያሳያቸው ሐዋርያት እኒህ ሦስቱ ናቸው። (ማቴ 17፡
1) የሙክራቡ አለቃ ሴት ልጅ በሞተች ጊዜ ሊያስነሳት ወደ ቤት ሲገባ እነዚህን ሦስት ሐዋርያት አስከትሎ
ነበር የገባው። በጌቴ ሴማኒ የአትክልት ቦታ በሚጸልይ ጊዜ እኒህን ሦስት ሐዋርያት ነበር ይዞ
የሄደው።(ሉቃ 26፡37)። እነዝህ ሦስት ሐዋርያት ከዘጠኙ የበለጠ ምሥጢር የሚያዩ ነበሩ። አዕማድ
የሆኑት በዚህ ምክንያት ነው። ሆኖም ግን እግዚአብሔር በሐዋርያቱ መካከል አድልዎ አያድርግም
ሥራዓትን መሥራቱ ነበር እንጂ። ሐዋርያው ጳውሎስ በደማስቆ መንገድ ላይ ለሐዋርያነት ሲሾም እነዚህ
ሦስት ሐዋርያት አያውቁም ነበር ነገር ግን በአሕዛብ መካከል ይሰብክ የነበረውን ወንጌል ይሰሙ ነበር።
አንድ ቀን ግን በበርናባስ አስተዋዋቂነት በኢየሩሳሌም ተገናኝተው ስለ ወንጌል እውነት ተወያዩ። በዚህ
ጊዜ ለጳውሎስ የተሰጠውን ጸጋ አስተዋሉ እግዚአብሔር ለአሕዛብ የሾመው ሐዋርያ እንደሆነ ተገነዘቡ።
ጳውሎስ የሮሜ ዜግነት ስለነበረው የአሕዛብን ልማድ ጠንቅቆ ያውቃል። ስለዚህ የአሕዛብ ሐዋርያ ሆኖ
ተሾመ ይህ ማለት ግን የአሕዛብ ሐዋርያ ብቻ ማለት ሳይሆን አብዛኛውን የአገልግሎቱን መሥመር በዚያ
አደረገለት ማለት ነው።ጴጥሮስ ደግሞ የአይሁድን ልማድ ስለሚያውቅ አይሁድን እንዲያገለግል
አብዛኛውን አገልግሎት ለአይሁድ እንዲያደርገው መሥመሩን በዚያ ሠራለት።
ጳውሎስ ለአይሁድ የሆነው ወንጌል፤ ለአሕዛብ የሆነው ወንጌል ሲል አቀራረቡ እንደልማዳቸው የሆነ
ጳውሎስ ለአይሁድ የሆነው ወንጌል፤ ለአሕዛብ የሆነው ወንጌል ሲል አቀራረቡ እንደልማዳቸው የሆነ
ለማለት እንጂ የተለያየ መልእክት ያለው ወንጌል ተቀበልን ለማለት አይደለም። ወንጌል ሰማያዊ የሆነ
አንድ መልእክት አለው መልእክቱም በክርስቶስ የሆነ የዘለዓለም ሕይወት ነው። መጥፎውን፤ ባዕድ
አምልኮ ያለበትን ልማድ እና ባሕል እንጂ ጥሩውን ፤ በጎ የሆነውን እና ጉዳት የሌለውን ልማድ
አያፈርስም። በተለይም በአሕዛብ እና በአይሁድ መካከል የነበረው ልዩነት የመብል ጉዳይ ስለነበር
እግዚብሔር የመብል ልማዳቸውን መሠረት አድርጎ ሳይሆን ፍቅሩን ብቻ መሠረት አድርጎ በጸጋው
ሁለቱንም ተቀብሏቸዋል (ሮሜ 14፡1-5) ስለዚህ አይሁድ የማይበሉትን እንዲበሉ አይገደዱም አሕዛብም
የሚበሉትን እንዲተው አይገደዱም ይህ የባህል እንጂ የወንጌል ጉዳይ አይደለም።
እግዚአብሔር አድራሻችንን ሁኔታችንን ባህላችንን ያውቃል በዚህ እንዳለን ግን አንዱን የወንጌል እውነት
በአድራሻችን ባለንበት ባህል እና ሐገር ልኮልናል። ለአይሁድ ጴጥሮስን ለአሕዛብ ደግሞ ጳውሎስን
ልኮአል። ለእኛም ለኢትዮጵያውያን ባለንበት ሥፍራ ባለንበት ባህል ወንጌልን ልኮልናል። ታዲያ በወንጌል
እውነት የሕይወጥ ለውጥ እንዲመጣ መስበካችንን ትተን የባህል ለውጥን የምንሰብክ ከሆነ ብጥብጥን
እንጂ ሰላምን አናመጣም። አንዳዶች የባህል ለውጥን ለማምጣት ሲታገሉ የወንጌልን እውነት የረሱት
ይመስለኛል ለዚህ ነው የባህል ለውጥ እንጂ የሕይወት ለውጥ ማየት ያልቻልነው። እግዚአብሔር
አይሁድን በአይሁድነታቸው አሕዛብን በአሕዛብነታቸው በክርስቶስ በኩል ከተቀበለ። እኛን
ኢትዮጵያውያንንስ በኢትዮጵያዊነታችን በክርስቶስ በኩል እንዴት እንዲያው አይቀበለን? ታዲያ ከባህል
ለውጥ ጋር ግብ ግብ ከመግጠም ከሌላው የጥላቻ እና የክፋት ኃይል ጋር መዋጋት አይሻልምን? አዕማድ
ሐዋርያት የእግዚአብሔርን አሠራር ተረድተዋል እነርሱ ወደ ተገረዙት ጳውሎስ እና በርናባስ ደግሞ ወደ
አሕዛብ እንዲሄዱ ቀኝ እጃቸውን ሰጡአቸው (ቁ. 9)። ቀኝ እጅን መስጠት ስምምነትን ያመለክታል ቀኝ
እጅ ለወዳጅ እንጂ ለጠላት አይሰጥምና ። የወንጌል እውነት ያስማማል የወንጌል እውነት ከሌለን ግን
የቱንም ያህል ብንቀራረብ አንድ ልብ ሊኖረን አይችልም።
ዛሬ በዚህ ዘመን ያለን ክርስቲያኖችም ሌላውን የርስ በርስ ጦርነት እንተወውና በወንጌል እውነት ላይ
እንስማማ የወንጌልን እውነት ለዓለም እንንገር ያልተላክንበትን ስናወራ የተላክንበትን መርሳት የለብንም።
ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ ተብለናል። ጴጥሮስ እና ጳውሎስ በአንድ ወቅት በወንጌል እውነት
ምክንያት ተጋጭተው ነበር። ጴጥሮስ አይሁድ በማይኖሩበት ጊዜ ከአሕዛብ ጋር አብሮ ይበላል አይሁድ
በሚመጡበት ጊዜ ደግሞ በነገሩ እንዳላመነበት ለማስመሰል ከአሕዛብ ይለያል። በብሉይ ኪዳን ዘመን
አይሁድ ከአሕዛብ ጋር አይተባበሩም ነበር። አሁን ግን ያ የጥል ግድግዳ በክርስቶስ ደም መፍረሱን እና
ሁለቱ በክርስቶስ አንድ መሆናችውን ወንጌል ይናገራል
"ስለዚህ እናንተ አስቀድሞ በሥጋ አሕዛብ የነበራችሁ፥ በሥጋ በእጅ የተገረዙ በተባሉት ያልተገረዙ
የተባላችሁ፥ ይህን አስቡ፤ በዚያ ዘመን ከእስራኤል መንግሥት ርቃችሁ ለተስፋውም ቃል ኪዳን
እንግዶች ሆናችሁ በዚህም ዓለም ተስፋን አጥታችሁ ከእግዚአብሔርም ተለይታችሁ ያለ ክርስቶስ
ነበራችሁ። አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም
ቀርባችኋል። እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ የተነገሩትንም የትእዛዛትን ሕግ ሽሮ
በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፤ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ
ይፈጥር ዘንድ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፥ ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል
ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው። መጥቶም ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን፥ ቀርበው
ለነበሩትም ሰላምን የምስራች ብሎ ሰበከ፤ በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት
አለንና። እንግዲያስ ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሔር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ
እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም" (ኤፌ 2፡11-19)።
እንግዲህ ቅዱስ ጴጥሮስ ለዚህ የወንጌል እውነት ጸንቶ ሊቆም ባለመቻሉ ቅዱስ ባውሎስ ፊት ለፊት
ተቃውሞታል እንዲያውም ፍርድ ይገባው ነበር በማለት ይናገራል። ጴጥሮስ አይሁድን ሲያይ እንደ
አይሁድ አሕዛብን ሲያገኝ እንደ አሕዛብ መሆኑ ከመካከላቸው የተወገደውን የጥል ግድግዳ እና
በክርስቶስ የተመሠረተውን ሰላም የሚሸረሽር ነበር። በመሆኑም ጳውሎስ ባይቃወመው ኖሮ ይህ የወንጌል
እውነት በሁለቱ ማለት በአይሁድ እና በአህዛብ ዘንድ ሥፍራውን ባጣ ነበር። በርናባስም በዚህ አይነቱ
እውነት በሁለቱ ማለት በአይሁድ እና በአህዛብ ዘንድ ሥፍራውን ባጣ ነበር። በርናባስም በዚህ አይነቱ
ግብዝነት ትስቦ ነበር። ወንጌል ግን እውነት ነውና ያሸንፋል።
“አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤
ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና። እናንተም የክርስቶስ ከሆናችሁ እንኪያስ የአብርሃም
ዘር እንደ ተስፋውም ቃል ወራሾች ናችሁ” (ገላ 3፡28-29)።
የሚለው የወንጌል እውነት ነው። ይህ አንድነት የመጣው በክርስቶስ ደም ነው። ስለዚህ እንደገና የጥል
ግድግዳን መሥራት የክርስቶስን ደም ከንቱ ማድረግ ነው። እኛም በዚህ ዘመን የምንገኝ ክርስቲያኖች
በሚያምኑ እና የክርስቶስ አካል በሆኑ የእግዚአብሔር ልጆች መካከል በባህላቸው እና በሥራዓታቸው
ምክንያት ጠብና ጥላቻን መገንባት የለብንም። ሁሉም ወደ እግዚአብሔር የመጣው በክርስቶስ እንጂ
በባህሉ እና በዘሩ አይደለም እንጠንቀቅ።
እኛ በፍጥረት አይሁድ ነን ኃጢአተኞችም የሆኑ አሕዛብ አይደለንም (ቁ. 15)(... ይቀጥላል)

ባሪያዎች ሊያረጉን (የገላትያ መልእክት ም 2፡4-5 (ክፍል ፪) ዲ. ተከስተ ጫኔ

ባሪያዎች ሊያረጉን (የገላትያ መልእክት ም 2፡4-5 (ክፍል ፪)

የወንጌል እውነት ምንድን ነው?
“የወንጌልም እውነት በእናንተ ዘንድ ጸንቶ እንዲኖር አንድ ሰዓት እንኳ ለቀን አልተገዛንላቸውም” (ገላ 2፡5)።
ጳውሎስን በጽናት ሊያቆመው የቻለው የወንጌል እውነት ነው። ሰው እውነትን አረጋግጦ ካልያዘ በትንሽ ነገር
ሊወድቅ ይችላል። እውነትን የያዘ ሰው የምሥክርነት አቋም ብቻ ሳይሆን በያዘው እውነት ላይ የመኖር ችሎታ
አለው። ለምሳሌ እምነቱ በሚሰጠው ትርጉም መሠረት ቅድስና ጽድቅ ፍቅር እና ሰላም ዋና ሕይወቱ ናቸው።
ጳውሎስም ከአይሁድ ጋር ስለአለው የሁለቱ ኪዳናት ክርክር ብቻ ሳይሆን በጽድቅ እና በቅድስናም ጸንቶ የኖረ
ሰው ነው። የወንጌል እውነት በሚመሰክርላቸው ሰዎች ጸንቶ የሚኖረው ስለ ወንጌል ባለው እውቀት መታገሉ
ብቻ ሳይሆን ሙሉውን የወንጌል እውነት በሕይወቱ ሲገልጠው ጭምር ነው።
እኛም ዛሬ በዚህ ዘመን የምንገኝ ክርስቲያኖች የወንጌልን እውነት በትክክል መረዳት እና በጽናት መቆም
አለብን። ይህን የወንጌል እውነት እንደሚከተለው ለመግለጥ እሞክራለሁ።
የወንጌል እውነት “ክርስቶስ ኢየሱስ ኃጢአተኞችን ሊያድን ወደ ዓለም መጣ” የሚለው ቃል ነው (1ጢሞ 1፡
15)። በዚህ ቃል ውስጥ ትኩረት ሰጥተን የምንመለከታቸው:
* “ወደ ዓለም መጣ”
* “ኃጢአተኞችን ሊያድን”
የሚሉትን ቃላት ነው።
ወደ ዓለም መጣ: ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን የፈጠረ፤ በሰማይ እና በምድር ያሉትን ሁሉ ያዘጋጀ ፈጣሪ ነው
(ዮሐ 1፡1-3, ቈላ 1፡15-18)። በመለኮቱ ከአብ ጋር የሚተካከል የአብ ልጅ ነው። ወደ ዓለም በሥጋ ከመምጣቱ
በፊት በዓለም የነበረ ነው። ይህ የወንጌል እውነት ነው።
“ለሰው ሁሉ የሚያበራው እውነተኛው ብርሃን ወደ ዓለም ይመጣ ነበር፤ በዓለም ነበረ፤ ዓለሙም በእርሱ ሆነ
ዓለሙም አላወቀውም” ይላል (ዮሐ 1፡9-10)።
ወደ ዓለም መጣ ማለት በሥጋ ፍጹም ሰው ሆኖ ተገለጠ ማለት ነው ስለዚህ ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰው
ፍጹም አምላክ ነው። ይህ የወንጌል እውነት ነው። ይህን የወንጌል እውነት የማያምን ሰው ክርስቲያን ነኝ
ማለት አይችልም ይህን የማያስተምርም ከእግዚአብሔር አይደለም።
ኃጢአተኞችን ሊያድን: ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዓለም የመጣበት ዋና ነገር ኃጢአተኞችን ሊያድን ነው።
በአዳም በደል ምክንያት ዓለም ሁሉ ኃጢአተኛ በመሆኑ የእግዚአብሔር ፍርድ አለበት። በዚህ ምክንያት
ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለምን ፍርድ ተሸክሞ በመስቀል ላይ ሞተ። ዮሐንስ “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘለዓለም
ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ አለሙን እንዲሁ
ወዶአልና” ይላል (ዮሐ 3፡16)። ስለዚህ ዓለም የዳነው እንዲሁ እግዚአብሔር ስለወደደው እንጂ የሙሴን ሕግ
ስለፈጸመ አይደለም ይህም ጸጋ ይባላል። ክርስቶስም በሕግ ላይ የተመሠረተውን ኪዳን ሳይሆን በራሱ ደም
የተመሠረተውን ኪዳን ሠጥቶናል (ማቴ 26፡27)። ኃጢአተኞች በእግዚአብሔር ጸጋ እንጂ በሙሴ ሕግ ሊድኑ
አይችሉም። ጳውሎስ ለአንድ ሰዓት እንኳ ሳይለቀው ጸንቶ የቆመበት የወንጌል እውነት ይህ ነው።
ኢየሱስ ክርስቶስ የነቢያትን አገልግሎት ወርሶ ነቢይ መሆኑ (የሐዋ 3፡22)።
የዳዊትን ዙፋን ወርሶ ንጉሠ ነገሥት መሆኑ (ሉቃ 1፡35)።
የአሮንን ክህነት ወርሶ በመልከጸዴቅ ምሳሌ ለዘለዓለም ሊቀ ካህናት መሆኑ (ዕብ 7፡1-8፤ 8፡13)። የወንጌል
እውነት ነው።
በሞቱ ሞትን ካጠፋ በኋላ ከመቃብር ተነሥቶ ማረጉ በአብ ቀኝ መቀመጡ እና ዳግም ለፍርድ የሚመጣ መሆኑ
የወንጌል እውነት ነው።
ይህ እውነት በሐሰተኛ አስተማሪዎች እንዳይጣመም ጳውሎስ ከፍተኛ ተጋድሎ አድርጓል ተደብድቧል፤
ተገርፏል፤ ተርቧል፤ ተጠምቷል፤ ተስዷል በያዘው እውነት ላይ ዋጋ ከፍሏል። ውንጌልን ከግዝረት እና
ከሌሎች ሕጎች ጋር ቀላቅለው ሊሰብኩ የሚወዱ ፈሪሳውያንን በጽናቱ አሸንፏል። ጌታ ከፈሪሳውያን እርሾ
ተጠበቁ ያለው ከትምህርታቸው ተጠንቀቁ ለማለት ነበር (ማቴ 16፡5-12)።
እኛም ከፈሪሳውያን ትምህርት አስተሳሰብ እና ፍልስፍና መጠንቀቅ አለብን። በዚህ ዘመንም ክርስቲያን
የሚመስሉ ፈሪሳውያን ሊኖሩ ይችላሉ።እነርሱንም ለይቶ ለማወቅ ከባድ አይደለም ግዝረትን እና ሌሎች ልዩ
ልዩ ኦሪታዊ የሆኑ የሥጋ ሥርዓቶችን ከወንጌል ጋር ቀላቅለው ሲሰብኩ መስማት ይቻላል። እነዚህ አደገኛ
ሐሰተኞች በመሆናቸው በትምህርታቸው እንዳንወሰድ መጠንቀቅ አለብን። የወንጌልን እውነት ያልተረዱ
የዋሃን የሆኑትን ግን ለማስረዳት መሞከር እንጂ መሸሽ ወይም ማሳደድ የለብንም። ይህ ማሳደድ የወንጌል
እውነት አይደለም።
ጸንተን እንቁም!!
በወንጌል ማፈር የለብንም ልንሰደድ፤ ልንገረፍ፤ እንችላለን ነገር ግን ያመንበት ወንጌል እውነት እና ንጹሕ
ስለሆነ ልንሸቃቅጠው አይገባንም። ልንናገረው የማንችል ከሆነ ዝም ማለት ይሻላል እንጂ የሚደርስብንን
የዓለም ተጽእኖ በመፍራት እውነት ያለሆነ ነገር ብንቀላቅልበት ከባድ ቅጣት የጠብቀናል። ጌታ እንክርዳዱን
ከስዴው ለይቶ ወደ እሳት እንደሚጥለው የተናገረውን ቃል መርሳት የለብንም። (ማቴ 13፡40)።
ሌላው የወንጌል እውነት: ሌላው የወንጌል እውነት ሰላም ደስታ ፍቅር ቅድስና ምህረት እና ጽድቅ ወዘተ
የመሳሰለው ነው። እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን በጸጋው ያዳናቸው በኃጢአታቸው ጸንተው እንዲኖሩ
አይደለም። ከኃጢአታቸው ተላቀው የጽድቅ እና የቅድስና ኑሮ እንዲኖሩ ነው እንጂ።
የእግዚአብሔር ጸጋ ኃጢአተኝነትን የሚያስወግድ እንጂ ልቅነትን የሚያበረታታ የሥጋን ኑሮ የሚያመቻች ልዩ
ፈቃድ አይደለም።
ሐዋርያው ጳውሎስ ስለእግዚአብሔር ጸጋ ሲናገር “ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጧልና
ይህም ጸጋ ኃጢአተኝነትን እና ዓለማዊ ምኞትን ክደን የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን
የአምላካችንንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን እራሳችንን በመግዛትና
በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል” ይላል (ቲቶ 2፡11-13)። እራስን
መግዛት፤ የጽድቅን ኑሮ መኖር እንዲሁም እግዚአብሔርን መምሰል የወንጌል እውነት ነው።
ወንጌል የሚባለው የክርስቶስ ሕይወት ነው በሌላ አነጋገር ክርስቶስ በምድር ላይ የኖረው ኑሮ ወንጌል ነው።
ይህን እውነት በጥሩ አነጋገር መናገር ይቻል ይሆናል የምንናገረውን የማንኖረው ከሆነ ግን እኛን የሚሰሙ
ሰዎች በወንጌል እውነት ጸንተው ሊኖሩ አይችሉም።
ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ሊታይ ይፈልጋል እኛ ክርስቲያኖች ግን የወንጌልን እውነት ባለሞኖር ግርዶሽ መሆን
የለብንም። እግዚአብሔር የገለጠውን እውነት፤ መንገድ ሕይወት የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን የጋረዱ ሁሉ
ወዮላቸው። ኃጢአተኝነት እና ዓለማዊ ምኞት ኢየሱስ ክርስቶስ በሕይወታችን እንዳይገለጥ የሚከለክል
ግርዶሽ ነው።
በእኛ እና በዓለም መካከል ልዩነት መኖር አለበት ይህም ሊሆን የሚችለው በወንጌል እውነት ጸንተን ስንኖር
ነው። የጽድቅ እና የቅድስና ኑሮ ከዓለም የምንለይበት ዋና ነገር ነው። አለባለዚያ ኢየሱስን እወቁ የሚለው
ስብከታችን ባዶ ጩኸት ሆኖ ይቀራል።
“በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት
የሚገባ አይደለም” ይላል (ማቴ 7፡21)። ይህም የወንጌል እውነት ነው። ትክክለኛውን እረፍት የምናገኘው
የእግዚአብሔርን ፈቃድ ስናደርግ ነው። የእግዚአብሔር ፈቃድ መቀደሳችን ነው ያለ ቅድስና እግዚአብሔርን
ማየት እንደማንችል ተጽፏል “ትቀደሱም ዘንድ ፈልጉ ያለ እርሱ ጌታን ሊያይ የሚችል የለምና የእግዚአብሔር
ጸጋ ለማንም እንዳይጎድለው” ይላል (ዕብ 12፡14)። ልባችንን ለእግዚአብሔር እንስጠው ይህ ማለት በወንጌል
እውነት ጸንተን ለመቆም እንወስን ማለት ነው።
አለቆች የመሰሉት ግን በፊት ማን እንደነበሩ አይገደኝም እግዚአብሔር የሰውን ፊት አይቶ አያዳላም
አለቆች የመሰሉት አንዳች እንኳ አልጨመሩልኝምና (ቁ. 6) (... ይቀጥላል)

ባሪያዎች ሊያደርጉን (ዲ. ተከስተ ጫኔ)

የገላትያ መልእክት ም 2፡4-5

ነገር ግን ባሪያዎች ሊያደርጉን በክርስቶስ ኢየሱስ ያለንን አርነታችንን ይሰልሉ ዘንድ
ሾልከው በስውር ስለ ገቡ ስለ ሐሰተኞች ወንድሞች ነበረ። የወንጌልም እውነት
በእናንተ ዘንድ ጸንቶ እንዲኖር ለአንድ ሰዓት እንኳ ለቅቀን አልተገዛንላቸውም። (ገላ
2፡4-5)።
ባሪያ መሆን ከባድ ነው። ባርነት በጥንት ዘመን እራስን የማጣት ያህል አስከፊ ነበር። ባሪያ
የጌታው ንብረት ነው። በቤት ውስጥ እንዳለ እንደ አንድ ጠቃሚ እቃ ወይም እንሥሣ እንጂ
እንደ ሰው ሆኖ በክብር አይታሰብም ነበር። ባሪያ ለጌታው ሥራ በሚሠራበት ጊዜ የታዘዘውን
ማድረግ ብቻ እንጂ ለምን ጉዳይ ያን እንደሚያደርግ መጠየቅ አይፈቀድለትም ነበር። “ ባሪያ
ጌታው የሚያደርገውን አያውቅም” ይላል (ዮሐ 15፡15)። ይህ ዓይነቱ ባርነት መንፈስን
የሚጎዳ ሥርዓተ ባሪያ ቢሆንም የሥጋ ባርነት ነው።
በጣም አስከፊው ባርነት ግን የመንፈስ ባርነት ነው በተለይም ሕይወትን በማይሰጥ ሃይማኖት
በሚመስል ወግ እና ልማድ መታሠር አስከፊ ባርነት ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ “ባሪያዎች
ሊያደርጉን በክርስቶስ ኢየሱስ ያለንን አርነት ሊሰልሉ” ሲል በትክክል ሰው ሊፈጽመው እና
ሊጸድቅበት በማይችለው በሙሴ ሕግ በማሠር በክርስቶስ ያገኘነውን የሕይወት ነጻነት
ሊያሳጡን ይፈልጋሉ ለማለት ነው።
ሐዋርያው ቅ/ጴጥሮስ በኢየሩሳሌሙ ሲኖዶስ ላይ ስለሙሴ ሕግ ሲናገር እንዲህ ነበር ያለው
“እኛ እና አባቶቻችን ልንሸከመው ያልቻልነውን ቀንበር በደቀ መዛሙርት ጫንቃ ላይ
በመጫን እግዚብሔርን አሁን ስለምን ትፈታተናላችሁ?” (የሐዋ 15፡10)።
አይሁድ አባቶቻቸው እና እነርሱ ያልቻሉትን ቀንበር በገላትያ ክርስቲያኖች ላይ ለመጫን
ሞክረው ነበር። ቀንበር በሬ የሚጠመድበት እቃ ሲሆን በሬው ቀንበር ውስጥ ከገባ በኋላ
ምንም ነጻነት ስለሌው አንገቱ እስኪመለጥ ድረስ የማይችለውን ሁሉ ሲጎትት ይውላል።
መንፈሳዊ ነገርም ሕግ እና ግዴታ ሲበዛበት ቀንበር ሆኖ የማይቻል ነገር ይሆናል። ሰዎችም
ከዚህ ቀንበር ውስጥ ላለመግባት ሲሉ ከሃይማኖት ይሸሻሉ። የገቡትም ቀንበሩ ሲከብዳቸው
የተለያየ ምክንያት በመደርደር በኃጢአት ይወድቃሉ። ከክርስቶስም ይሸሻሉ ከዚያም
የኃጢአት ባሪያ ሆነው ይኖራሉ። በክርስቶስ ያላቸውን አርነት ያጣሉ። በፍቅር እና በደስታ
ሳይሆን በግዴታ የሚደረግ ማንኛውም ነገር ባርነት ነው።
ክርስቶስ ከምንድር ነው ነጻ ያወጣን?
* በመጀመሪያ ከኃጢአት ባርነት ነጻ አውጥቶናል “ኃጢአትን የሚያደርግ የኃጢአት ባሪያ
ነው”(ዮሐ 8፡34)። እንደተባለ ኃጢአተኛ ባሕርያችን በአዲስ ልደት፤ በአዲስ ተፈጥሮ
ስለተዋጠ የኃጢአት ባሪያ ከመሆን ነጻ ወጥተናል ይህን ያደረገውም የክርስቶስ ጸጋ ነው።
ኃጢአትን እንዳናደርግ ብናደርግም እንኳ ንስሐ እንድንገባ የሚያስችል ኃይሉን ሰጥቶናል።
ኃጢአት እረፍት አይሰጥም ሰላምም የለውም ክርስቶስ ግን ከኃጢአት ነጻ በማውጣት እረፍት
እና ሰላምን ሰጠን።
* ሁለተኛ በሕግ ምክንያት ከሚመጣ የሞት ፍርድ ነጻ አወጣን። በሮሜ 7፡10 ላይ “ለሕይወት
የተሰጠችውን ትእዛዝ [ሕግ]ለሞት ሆና አገኘኋት” እንዳለ። ሕግ ለሕይወት ቢሰጥም ሰው
ከባሕርዩ የተነሳ መፈጸም ስለተሳነው የሚጸድቅበት ሳይሆን የሚሞትበት ሆነ። ስለዚህ
ኢየሱስ ክርስቶስ የኛን ሞት በመሞት የሕግ ፍጻሜ ሆኖ ነጻ አወጣን።
“የእግዚአብሔርን ጽድቅ ሳያውቁ የራሳቸውንም ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር
ጽድቅ አልተገዙም። የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና"
ይላል። (ሮሜ 10፡3-4)። በደብረ ሲና የተሰጠው ለሞት ሲሆን በቀራንዮ ላይ እራሱን የሰጠው
ክርስቶስ ግን ሕይወትን ሰጠን።
* ሦስተኛ ከሠይጣን ክስ እና እሥራት ነጻ አወጣን። ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር ብርሃን ሆኖ
ከመምጣቱ በፊት በጨለማ ውስጥ ነበርን። ሰይጣንም ጨለማውን ተገን አድርጎ የራሱን
አገዛዝ ይጭንብን ነበር ኤፌ 2፡1-3። አሁን ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንረግጠው ዘንድ
ሥልጣን አገኘን። “ያመኑትንም እንዚህ ምልክቶች ይከተሉአቸዋል በስሜ አጋንትን ያወጣሉ”
ይላል።(ማር 16፡17)። በስሙ ከሰይጣን እሥራት ነጻ ወጥተናል።
ነገር ግን ሰው ቀንበር ሲከብድበት መንፈሳዊ ኃይሉ ይደክማል ከዚያም ሊያድነው የማይችል
ሕግን ሁሉ ያወጣል በኃጢአትም ይወድቃል፤ በመጨረሻም በራሱ መንገድ እረፍት ሲያጣ
ተስፋ ይቆርጥና ከክርስቶስ ተለይቶ ይኖራል። እንዴት ያሳዝናል?
እንግዲህ ሐዋርያው “ባሪያዎች ሊያደርጉን በክርስቶስ ያለንን አርነት ሊሰልሉ” ሲል
አይሁድ በኢየሩሳሌሙ ጉባኤ ላይ በሐዋርያት ከተረቱ በኋላ በሥውር ሾልከው ወደ ገላትያ
እና ወደ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት በመግባት የሙሴን ሕግ ያስተምሩ ነበር። ይህንም
የሚያደርጉት ክርስቲያኖችን ለእግዚአብሔር ባሪያ ከመሆን አስወጥተው የራሳቸው ባሪያ
ሊያደርጓቸው ስለሚፈልጉ ነው። ጳውሎስ እንዲህ ዓይነቱን ውድቀት ለመከላከል እና
በክርስቶስ ላይ ያላቸውን እምነት በማጠንከር የእግዚአብሔር ባሪያዎች እንዲሆኑ ለማደረግ
ከፍተኛ ተጋድሎ አድርጓል።“የውንጌልም እውነት በእናንተ ጸንቶ እንዲኖር ለአንድ ሰዓት
እንኳ ለቀን አልተገዛንላቸውም” ይላል (ገላ 2፡5)። እኛም አርነታችንን አሳልፈን ላለምሰጠት
መጠንቀቅ አለብን። በክርስቶስ ያለንን አርነት ካጣን የኃጢአት ባሪያዎች ልንሆን ስለምንችል
የወንጌልን እውነት ጠንቅቀን ማወቅ አለብን።
የወንጌል እውነት ምንድን ነው? (... ይቀጥላል)

Wednesday, February 9, 2011

ገለባ ውስጥ የተደበቁትን ሁሉ ትንሽ እሳት ያስፈራቸዋል(aba Selama)

ገለባ ውስጥ የተደበቁትን ሁሉ ትንሽ እሳት ያስፈራቸዋል

ከፍርሐት፣ ከሥጋትና ከጭንቀት ነጻ ሆነው የሰላም እንቅልፍ ተኝተው ማደር የሚችሉት እውነትን የያዙና የሰው ደም የሌለባቸው ንጹሐን ብቻ ናቸው። ቃኤል ወንድሙን አቤልን ያለምንም ምክንያት ከገደለ ጀምሮ ፈሪና ተቅበዝባዥ ሆኖ ትንሽ ኮሽታ ሲያስደነግጠው የኖረ ሰው ነው። ይህ የሆነበት ምክንያት የአቤል ደም ወደ እግዚአብሔር በመጮኹ ነበር። ዘፍ 3፡10። የጻድቅ ደም እንቅልፍ አያስተኛም።
ዳንኤልን ያለምንም በደል በተራቡ የአንበሶች ጉድጓድ ውስጥ ያስጣለው የጥንቷ የባቢሎን የዛሬዋ ኢራቅ ገዢ የነበረው ሜዶናዊው ዳርዮስ እንቅልፍ አጥቶ ምግብም አልበላ ብሎት ሰላሙን አጥቶ አልጋው አልመቸው ብሎ ሲሰቃይ እንዳደረ ት/ዳን 6 ቁ 18 ላይ ይናገራል። ነቢዩ ኢሳይያስ ለክፉዎች ሰላም የላቸውም ይላል ኢሳ 57 ቁ 21። የሰው ደም እንደ ውሃ ሲያፈሱ፣ ጻድቁን ሲኮንኑ፣ ኃጥኡን ሲያጸድቁ በፕሮፓጋንዳቸው ተሰውረው ትንሽ እድሜ ያገኙ ሁሉ ሰላም የላቸውም።
በአሁኑ ሰዓት ይህን መጻፍ የፈለግሁት አንዳድ ቡድኖች በተለኮሰባቸው የነጻነት እሳት የሚይዝቱን እና የሚጨብጡትን አጥተው እየተወራጩ ስለሆነ ወገኖቼ የፕሮፓጋንዳቸው ሰለባ እንዳይሆኑ ለመከላከል ነው። እነዚህን ገለባ ውስጥ የተደበቁትን የደም ሰዎች እንደሚከተለው አቅርቢያቸዋለሁ።
1ኛ ኢሕአዴግ
ይህ ፓርቲ ከተመሠረተ ጀምሮ ያፈሰሰው ደም ወደ ላይ እየፈሰሰ አንገቱ ደርሶ እያነቀው በሞት ፍርሐት ውስጥ የሚኖር ተስፋ የሌለው ፓርቲ ነው። ነገር ግን ጽዋው ገና ስላልሞላ በሕይወት ያለ ግዙፍ ፓርቲ ይመስላል። ኢሐዴግ የሕጻናት፣ የወጣቶች፣ የሽማግሌዎች፣ የምሑራን፣ የመሐይምናን፣ የባልቴቶች፣ የወታደሮች ወዘተ ደም ወደ እግዚብሔር እየጮኸበት እንቅልፍ ያጣ ድርጅት ነው። እውነተኛ ሰዎች ያስደነግጡታል በራሱ አይተማመንም፣ የቃየልን መንፈስ ተዋርሶ ስለሚጠንቁል ያገኘኝ ሁሉ የሚገለኝ ይመስለዋል።
ቃኤል አቤልን ከገደለ በኋላ ለእግዚአብሔር እንዲህ ሲል አመለከተ በምድር ኮብላይ እና ተቅበዝባዥ እሆናለሁ የሚያገኘኝም ሁሉ ይገድለኛል አለው እግዚአብሔር ግን ይህ ፍርሐቱ የፈራውን ሁሉ ሰው በተደጋጋሚ እንዲገል ስለሚያደርገው ቃየልን ያገኘው ሁሉ እንዳይገድለው ምልክት አደረገለት ይላል ዘፍ 3 ቁ 14-15። እግዚአብሔር ቃየልን ማንም እንዳይገድለው የሚጠብቀው ምልክት ባያደርግለትና ትንሽ እረፍት ባይሰጠው ኖሮ ቃየል የፈራውን ሁሉ በመግደል ሰዎችን በጨረሰ ነበር።
ኢሕዴግን ከአራት ኪሎ እንዳይወጣ በሩን ዘግቶ ባለፈ ባገደመው ላይ እየተኮሰ እንዲቆይ ያደረገው ያፈሰሰው የደም ብዛት ስለሚጮኽበትና ያገኘኝ ሁሉ ይገለኛል ከሚለው ፍርሐቱ የተነሣ ነው። ይህ የቃየል መንፈስ እንዴት ይወገድለታል?
ኢሕአዴግ ዲሞክራሲያዊ መንግሥት ነኝ እያለ ቢያወራም አስተማማኝ የሆነ መኖሪያ ቤት የሌለው ገለባ ውስጥ የሚኖር መሆኑን እራሱ ያውቀዋል። ስለዚህ ትንሽ እሳት እጅግ ያስፈራዋል። ለምሳሌ አረና የተባለውን የትግራይ ፓርቲ እጅግ ስለሚያስፈራው ፎርጅድ አረና ሰርቶ ዋናውን እውነተኛ ፓርቲ ለማፍረስ እየሠራ ነው። አረናን ለምን ፈራው? ሕውሐት በትግራይ ሕዝብ ስም ዘግናኝ በደሎችን የፈጸመ ኢትዮጵያን ወደብ አልባ ያደረገ፣ ባድሜን ፈርሞ የሰጠ፣ የትግራይን ምርጥ ልጆች [እነሐየሎምን]ያለምንም ምክንያት የገደለ፣ የትግራይን ሕዝብ ከጎረቤቶቹ ከኤርትራ፣ ከወገኖቹ ከአማራ፣ ከኦረሞ፣ ከሱማሌ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ብሔረሰቦች ጋር ያጋጨ ጠላት የፈጠረ ግፈኛ በመሆኑ ትግራይን ከሌሎች ብሔረሰቦች ጋር ሊያስታርቅና በጋራ በኩልነት በነጻነት እንድትኖር ሊያደርግ የሚችል ፓርቲ የወያኔን ግፍ ሊያጋልጥ የሚችል በመሆኑ ይፈራዋል። አረና ከኢትዮጵያውያን ጋር እንዴት መኖር እንደሚገባ የተረዳ ቀና ፓርቲ፣ ብሐራዊ እርቅን የሚደግፍ፣ አብሮ መኖር የሚፈልግ ይመስለኛል።
ወያኔ ግን በጠባዩ ነፍሰ ገዳይ ነው። እንደ አቤል ያለ ቀና ፓርቲን ስለሚመቀኝ መግደል አለብኝ ብሎ ያስባል። ኢሕአዴግ ማንም እንደማይገድለው እንደ ቃኤል ምልክት ካልተደረገለት ገና ብዙ ይገላል ባይ ነኝ። እናም የፖለቲካ ፓርቲዎች የሕውሃትን ፍርሃት ሊያስወግድ የሚችል ፖለቲካዊ መተማመኛ እንዲሰጡት ስል እማጸናለሁ። አጥፍቶን ከመጥፋቱ በፊት ያገኘው ሁሉ እንደማይገድለው ማረጋገጫ ያስፈልገዋል። በዚህ ወቅት ግብጽ ላይ የተለኮሰው እሳት ገለባ ቤት ውስጥ የሚኖሩትን የአፍሪካ አምባገነኖች እያስደነገጠ ነው። የኛው ሕዋሐትም ኑሮው በታላቅ ፍርሐትና በጭንቀት ነው። ከዚህ ሁሉ ለምን ከገለባ ቤት ወጥቶ እሳት ወደማያስፈራው ዲሞክራሲያዊ ጽኑ ቤት ሽግግር አያደርግም? እሳት በተነሳ ቁጥር ያዙኝ ልቀቁኝ እያለ ለምን ግራ ያጋባናል? ነፋሱ ወደ ኢትዮጵያ ከነፈሰ እሳቱ ፊቱን ማዞሩና ገለባውም መበላቱ የማይቀር ነው። ስለዚህ ገላባው ውስጥ ያላችሁ ሁሉ ከገለባው ውጡ።
2ኛ የሃይማኖት መሪዎች
የሃይማኖት መሪዎች የእግዚብሔርን ድምጽ ለሕዝብ ለማሰማት በእግዚአብሔር ወንበር ላይ የተቀመጡ የከበሩ ሰዎች ናቸው። ነገር ግን አቀማመጣቸው ለአደጋ አጋልጧቸዋል። መንግሥት መገሠጽ እግዚአብሔር ልብ ለሰጣቸው መሆኑን አውቃለሁ ስለዚህ ለምን አይገሥጹትም የሚል ፍርድ ለመናገር አልደፍርም። እኔም ከዚያ ቦታ ላይ ብቀመጥ ምን ላደርግ እንደምችል አላውቅምና በሰው ግፊት ሰማትነት እንዲቀበሉ አልመክርም። ነገር ግን መገጸሥ ባይችሉም ከኢሐዴግ ጋር መተባበራቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም። በልማት በመልካም አስተዳደር ቢተባበሩ ተገቢ ነው። እንደ ኢሕአዴግ ሆነው የኢሐዴግን ተቃዋሚዎች ንጹሐንን አሳልፈው መስጠታቸው ግን ከቃኤል ማህበር ውስጥ መገኘታቸውን ያመለክታል።
ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በአሜሪካ የሚገኙት ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ምርቆርዮስ 13 ጳጳሳትን በሾሙ ጊዜ የአዲስ አባባን አገልጋዮች በማዋከብ ሰላም ነስተዋቸው እንደነበር እናስታውሳለን። ዛሬም የዉጩ ሲኖዶስ ሲነሣ እንቅልፍ እንደማይወስዳቸው ብዙ ጊዜ ታዝበናል። ይህ ሁኔታ ቃኤል እና አቤልን እንድናስታውስ ያደርገናል ቃኤል ሰላም አልነበረውም አቤል ግን እረፍት ላይ ነበር። በውጭ ያለው ሲኖዶስ በውጩ ዓለም ያሉ ኢትዮጵያውያንን በማስተማር በመሰብሰብ አንድነቱን አጠናክሮ እሳት በሚተፉ ስባኪዎቹ ታጅቦ ወደ ኢትዮጵያ የመግባት ተስፋ ያለው ነው ይባላል። የአቡነ ጳውሎስ ሲኖዶስ ግን በ2009 ዓ.ም በተነሣው የውስጥ ክፍፍል ታላላቅ አባቶችን በሌሊት እንደ ወንበዴ ሲደባደብ ተስተውሏል። ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ከገለባው ውስጥ ሊወጡ ይገባቸዋል። በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ታላላቅ ቦታዎች ላይ ተሹመው የሚገኙት የኢሕአዴግ አባላት የሆኑት ስለሆኑ ሕዝቡ የሐይማኖት ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ እስራትም እንዲኖርበት እንዳይንቀሳቀስና ሃማኖታዊ ንቃት እንዳይኖረው እመቤቴ ታውቅላሃለች በሚል አጉል ተስፋ እንዲደነዝዝ ተደርጓል። ይህ ገለባ እሳት የበላው ቀን ወዮ!
3ኛ ማህበረ ቅዱሳን
ማህበረ ቅዱሳንን በየጽሑፋችን የምናነሳው ጥላቻ ስላለብን አይደልም። ኢትዮጵያን ወደ ኋላ እየጎተተ ያለ ለኢትዮጵያ የማይጠቅም አስተሳሰብ ይዞ ስለሚራመድ እንዲያስብብበት ለማድረግ ነው። አባላቱ ወንድሞቻችን ናቸው ነገር ግን አሳባቸው እጅግ በጣም የተባለሸ ነው። መንፈሳዊ ነገር የተማሩ ቢመስሉም ምንም የሚያውቁት አንዳች ነገር የለም። አባላቱ የማህበረ ቅዱሳን አባላት የሆኑት መንፈሳዊ ነገር ተረድተው ሳይሆን የፕሮፓጋንዳ ሰላባ በመሆናቸው ነው። የሚማሩት ሃይማኖታዊ ፖለቲካ እንጂ የእግዚአብሔርን ፈቃድ አይደለም። የሳይኮሎጂ ችግር ውስጥ ገብተዋል። ይህን ለማረጋገጥ አንድ ነገር እንድታስተውሉ ልጠቁማችሁ።
እነርሱ ባሉበት ሁሉ ሰላም የለም። ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሄዱ ለራሳቸው ማምለክ ሳይሆን የሚፈልጉት የሌሎችን አለባበስ፣ አዘማመር፣ ካህናቱ ቅዳሴ ገብተው እስኪወጡ ድረስ እንቅስቃሴያቸውን መከታተል፣ ቃጭሉ ምን ያህል ጊዜ እንደተመታ፤ መጋረጃው መቸ እንደተዘጋ እና እንዳልተዘጋ ማየት፤ የሁሉንም ምእመናን የአምልኮ ሁኔታ መቆጣጠር፤ ትክክል አይደለም ያሉትን ለማስተካከል በመከራከር የሃይማኖት ፖሊስ መሆን ይፈልጋሉ። በዚህ አሰልቺ ክርክራቸው ስንቱ ክርስቲያን እቤቱ ቀርቷል?። ሰርግ ላይ ሲገኙ ማን ምን እንደለበሰ የሚቆጣጠሩት ማህበረ ቅዱሳኖች ናቸው። በሰርጋቸው ላይ ከውሃ በቀር ሌላ እንዲጠጣ አይፈልጉም። በቬሎ የተጋቡ ሙሽሮችን አጥብቀው ያወግዟቸዋል።
በሰዎች ላይ መከፋፈልንና የሳይኮሎጂ ችግር ሊያመጣባቸው የሚችለውና ዋናው የማህበረ ቅዱሳን የፍርኃት ትምህርት ተሃድሶዎች እትዮጵያን ሊያጠፉ የመጡ ናቸው የሚለው ነው። ይህ ፕሮፓጋንዳ በኦርቶዶክሳውያን መካከል መተማመን እንዳይኖር ከሳሽ እና ተካሽ ሆነን እንድንከፋፈል አድርጎናል። ፍርሐትን እንጂ እምነትን አይማሩም፤ በዚህ ምክንያት በአብያተ ክርስቲያናት ሰላም ጠፍቷል እስከ አሁን ያልበረደው የአዋሳ ገብርኤል ብጥብጥ በማህበረ ቅዱሳን የሚመራ ነው። በአሜሪካ በዳላስ ሚካኤል ዱላ እስከመማዘዝ ደርሰዋል። የውጭው ሲኖዶስ ጨርሶ ስላባረራቸው በሰላም እየኖረ ነው ከዚያ በፊት ግን በነዳንኤል ክብረት አዝማችነት ከፍተኛ ሁከት ነበር።
ዛሬ በነሱ ላይ ለመጻፍ የተነሳሳሁበት ምክንያት ደጀ ሰላም በተባለው ጸረ ሰላም ድረ ገጻቸው ላይ የተሃድሶ ወጥመድ” የሚል ሐሳብ ያለው ጽሑፍ ካነበብሁ በኋላ ነው። ይህ ፕሮፓጋንዳ ኦርቶዶክሳውያን እርስ በርሳቸው እንዳይተማመኑ የሚያደርግ ተንኮል ስለሆነ ወገኖቼን ተተንቀቁ ለማለት ነው።
ኢሕዴግን ዲሞክራሲ የሚያስፈራውን ያህል ማህብረ ቅዱሳንንም ወንጌል ያስፈራዋል። ኢየሱስ የሚል ስም ያስደነግጠዋል፤ ወንጌል የኃጢአትን ቆሻሻ የሚያቃጥል እሳት መሆኑ የታወቀ ነው። ማህበረ ቅዱሳን ወንጌልን የሚፈራው ገለባ ውስጥ ተደብቆ ስለሚገኝ ነው። ገድላት እና ድርሳናት በሚል ጭፍን ፕሮፓጋንዳ ይዘታቸውን የማያስተውለውን ሕዝብ በማሰለፍ የገንዘብ ምንጫቸው ስላደርጉት ወንጌል ሲሰበክ አይወዱም ኢየሱስ ጌታ አዳኝ የሚሉ ሰዎች ሁሉ ተሃድሶዎች ስለሆኑ አትስሟቸው ብለው አባላቱቹን አሳውረዋቸዋል።
እውነቱን የተረዱ ወጣቶች የቤተ ክርስቲያናቸውን ችግር ለይተው ያስተዋሉና ቤተ ክርስቲያናችንን አንለቅም ብለው የቤተ ክርስቲያናችን ምእመናን እውነቱን አውቀው ወደ ሌላ ሃይማኖት እንዳይፈልሱ በቅንነት እየተጉ ያሉትን ወገኖች ስማቸውን በመበከል መከራ ሊያመጡባቸው ይፈልጋሉ። ከሣቴ ብርሃን የተባለውን ኮሌጅ እና ቅድስት ሥላሴን መጥፎ ጥላሸት እየቀቡ ናቸው። እነዚህ የቤተ ክርስቲያናችንን ተስፋዎች ድርሳን እና ገድል ካላነበባችሁ ተብለው እንደዚህ የሚወገዙት ለምን ይሆን? እስልምና አገር እየወረረ ባለበት በዚህ አሳዛኝ ወቅት ሰባኪዎቻችንን ተቀባይነት እንዲያጡ የሚድረገው ሥራ ሰይጣናዊ ሥራ እንጂ ሌላ ፋይዳ አይገኝበትም።
እነዚህ ወንድሞቻችን ትምህርት ቤት የገቡት ከሕዝቡ የተሻለ አስተሳሰብ እንዲያገኙና ሕዝብን ካለበት ችግር እንዲያላቅቁ ታስቦ እንጂ ባሉበት ላይ እየረገጡ ጎታች ቡድኖች እንዲሆኑ አይደለም። የመንፈሳዊ ኮሌጆቻችን ተማሪዎች መለወጥ ለቤተ ክርስቲያናችን ተስፋ ነው። ዘኬ በመብላት ጊዜያቸውን ከሚያባክኑ 500000 [አምስት መቶ ሺህ] ካህናት ውስጥ የለውጥ ሰዎች ማግኘታችን እድሎኞች ያደርገናል እንጂ የሚጎዳን አይደለም። እነርሱ ቤተ ክርስቲያን በጥራት መጓዝ እንዲኖርባት ለማስተካከል የሚታገሉ እንጂ ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት እንዳልሆነ ለማንም ግልጽ ነው።
ማህበረ ቅዱሳን እውነት መስሎት ልጄ ልጄ እየተባለ ሲቆላመጥ በነበረበት ወቅት በትውልዱ ላይ ያን ሁሉ ቆሻሻ ትምህርት ዘርቶ አሁን እውነቱ እየወጣ ሲጋለጥ ስም በማጥፋት ጊዜውን ለማራዘም ይታገላል። ካፈርሁ አይመልሰኝ እንደሚባለው መረጃ አገኘሁ ሊያጠፉን ነው በማለት ይጮኻል።
በመሠረቱ ማህበረ ቅዱሳን ለተሰጡት አስተያየቶች መልስ መስጠት አለበት።  በ abaselama.org ላይ የቀረቡት ትችቶች መልስ አልተሰጠባቸውም።  የዶሮ ጭንቅላት መብላት እንደ ቅባ መንግሥት ሆኖ በገድለ ተክለሃይማኖት ላይ መገለጡ ከምን የተቀዳ ልምምድ ነው? ለሚለው ጠንካራና ግልጽ ጥያቄ መልስ መስጠት ያስፈልጋል ወይም መጽሐፉን አንቀበለውም የኛ አይደለም ማለትም አንድ መልስ ነው። ከዚህ አልፎ ግን ባዶ ፕሮፓጋንዳ መንዛት ያልበላውን ማከክ ነው። እውነቱን መደበቅ አይቻልም። ማህበረ ቅዱሳን እውነቱን በመሸሽ በፕሮፓጋንዳው እቀጥላለሁ ካለ ግን በተጨባጭ አሁን እየተደረጉ ያሉ አስከፊ የሚባሉ ሃይማኖታዊ ሽፋን ተሰጥቷቸው የሚፈጸሙትን ምሥጢራዊ ወንጀሎችን ወደ አደባባይ እንዲወጡ ያደርጋቸዋል። ይልቁንስ ተሃድሶ እያለ ከሚከሳቸው ወንድሞቹ ጋር በመወያየት ክርስትናው በኢትዮጵያ የሚስፋፋበትን መንገድ በጋራ መፈለግ፣ መታረም ያለባቸው እንዲታረሙ መርዳት፣ አጉል ኩራት አይሆንም እራት እንደተባለው የሁለት ሺህ ዓመት ታሪክ አለኝ የሚለውን ትምክህት ትቶ ዛሬ የጌታን ፈቃድ ቢፈጽም ይሻለዋል።
አንዳድ አስተያየት ሰጭዎች ተሃድሶዎች ኦርቶዶክስን ትተው ፕሮቴስታንቱን ለምን አያድሱም ይላሉ። እነርሱ ስለቤታቸው እንጂ ስለጎረቤታቸው የሚያገባቸው ነገር የለም የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች እንደተባለው መሆን አይፈልጉም።
ማህበረ ቅዱሳን እንደሚያወራው ተሃድሶዎች ቤተ ከርስቲያኒቱን ለማፈረስ ሳይሆን ከወደቀችበት ለማንሳት ትልቅ ሸክም ያለባቸውና ወደ ጥንታዊ ማንነቷ እንድትመለስ የሚደክሙ ናቸው።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!
በተስፋ አዲስ

Sunday, February 6, 2011

በምግብ መርከስ አለ?

ለክርስቲያኖች እንድንበላ የተፈቀደልን ምን አይነት ምግብ ነው? 
የፈለግነውን መብላት አለመብላት ያረክሳል ወይ (ሃጥያት ነው ወይ?)

Friday, February 4, 2011

king Nafkote (የስደተኛ ወላጅ ልዩ አደራ - e afe deqiq)

የስደተኛ ወላጅ ልዩ አደራ

ከአሜሪካ ቀደምት ሰፋሪዎቸ ቀጥሎ አይሪሾች እስራኤላውያን (ጁዊሽ) ሕንዶች እና ቻይናዎች ባህር አቋርጠው ወደ ምድረ አሜሪካ የተሰደዱ መጤዎች ናቸው።  ቀደም ብለው የመጡት ወላጆቻቸው አሁን አሁን የሉም ወይመ በጣም አርጅተዋል።  ልጆቻቸውና የልጅ ልጆቻቸው ግን እስራኤላዊ ማንነታቸውን ሳይለቁ አሜሪካዊ ሆነዋል ሕንድነታቸውን ሳይለቁ አሜሪካዊ ናቸው።  ቻይናዊ ቋንቋቸውን እና ባሕላቸውን ሳይተዉ ፍጹም አሜሪካውያን ናቸው።

የኛ ልጆችስ እንዴት ይሆኑ ይሆን? ኢትዮጵያዊ ልጆቻችን ማንነታቸውን እንደያዙ አሜሪካዊ ይሆናሉ ወይስ በታሪክ አጋጣሚ በግዞት ወደ አሜሪካ መጥተው ማንነታቸውን ማግኘት እስካይችሉ ድረስ ከወገናቸው እንደተነጠሉት አፍሪካ-አሜሪካውያን አዲስ ማንነት ፍለጋ ይባክናሉ? ወይስ በዓይናችን ፊተ እያደጉ ያሉት ልጆቻችን በኢትዮጵያዊ ማንነታቸው በኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖታቸው ላይ መልካሙን አሜሪካዊ እሴት ይገነባሉ ወይስ ከሃብትና ሀገር በስተቀር ይሄ ነው የሚባል ሃይማኖታዊ መሰረት ካልወረሰው ግብረሰዶማዊነት እንደ መብት ክህደትን እንደ ሳይንስ እምነትን እንደ ፋሽን ዝሙትን እንደ ነጻነተ ከሚቆጥረው ከንቱ የፈረንጅ ክፍል ጋር ይቀላቀላሉ?

ይህ እንዳይሆን ማድረግ የስደተኛ ወላጅ አደራ ነው።

ዘረ ኢትዮጵያውያን በሰሜን አሜሪካ ከአንድ ትውልድ የዘለለ እድሜ አላስቆጠርንም።  ፈተናው ግን ቀድሞን አሜሪካ ገብቷል።  አይሪሾች አልፈውታል ጁዊሺች አልፈውታል ህንዶችና ቻይናዎች እያለፉት ነው።

የኢትዮጵያዊነት መልካም እሴትና የቀና ሃይማኖት ጠብቆ አሜሪካዊ እሴትን የመዋኃድ ዓላማን ለማሳካት የስደት ዓለም የሚያስከፍለውን ዋጋ ሁሉ እየከፈሉ ልጆቻቸውን በማሳደግ ላይ ያሉ ወላጆች የተለየ ቦታ አላቸው።

ከሁሉ በላይ ደግሞ ልጆቻቸው ጥሩ ቦታ እንዲውሉ የተሻለ ትምህርት ቤት እንዲማሩ ስነ ልቦናቸው እንዳይጎዳ ወዘተ… ሲሉ የማይለመድ የሚመስለውን የኑሮ ዘይቤ ሀሉ ለምደው የሚኖሩ ወላጆች መስዋዕትነታቸው ከባድ ነው።  ፍሬ ግን የሚያፈራው እነርሱም እግዚአብሔርን ሲፈሩ ልጆቻቸውንም በዚህ መሰረት ላይ ሲገቡ ነው።  ይስሃቅ የመሰለ ልጅ ለማግኘት አብርሃምን መምሰል ያስፈልጋል።

መጀመሪያውኑ ልጆችን ለወላጆች በአደራ የሰጠ ራሱ እግዚአብሔር ነው ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸውና” መዝ 126፡3። ለወላጅ ዕድሜ ሰጥቶ ለልጆች ጠባቂ መልዐክ መድቦ የሚያኖረው እግዚአብሔር ነው።

የኦርቶዶክሳው ወላጅ የመጀመሪያ አደራ ልጆቹን ቤተ ክርስቲያን ማምጣት ነው። አምጥቶ ጌም እንዲጫወቱና ሙዚቃ እንዲሰሙ መተው አይደለም እንደአቅማቸው ለጥቂት ደቂቃ የቤተ ክርስቲያንን ጣዕም እንዲለዩ ማድረግ እንጂ። እጣኑን እንዲያሸቱ ቃጭሉን እንዲሰሙ ጠበሉን እንዲጠጡ ቄሳቸውን ጳጳሳቸውን እንዲያውቁ የማንነታቸውን መሰረት እንዲያውቁ። ልጆን በሚሄድበት መንገድ ምራው በሸመገለ ጊዜ ከእርሱ ፈቅቅ አይልም። ምሳ22፡6

ወስበሐት ለእግዚአብሔር።

Thursday, February 3, 2011

(The Early Church,KN)

In AD 33, after Jesus had lived his life, preached his message, performed his miracles, died, risen from the dead and ascended into heaven, Christianity was still a long way from being an organized 'Church' as we understand the term. How, then, did Christianity actually get started as an institution? Just what happened to the Christians - Jesus' friends, those who had heard him preach, those who heard the new doctrine from others, and all of the generations of Christians that followed them over the next two hundred and eighty years until Christianity was finally legitimized in AD 313?

We do not know very precisely. The new religion appealed largely to a small minority of the population of the Roman Empire - a predominantly poor, uneducated and powerless minority at that. Whenever Christianity did show signs of rising to greater prominence, it attracted the attention of the authorities, who viewed it as theologically, philosophically, socially and politically suspect and a threat to the status quo. They reacted by firmly and repeatedly quashing it. So Christians kept a very low profile, meeting in secret in people's houses, in out-of-the-way places in the countryside, or underground in catacombs.

What we do know about the first centuries of Christianity is mostly to be found in the New Testament of the Bible, written between AD 50 and 120, the writings of the Apostolic Fathers )the second- and third-generation Christians of the first century and the first half of the second century) and, ironically, through records of the verbal and physical attacks on Christians and Christianity by their detractors. Traces of early Christianity are also to be found in a few catacombs with early Christian art and artifacts - fortunately and wonderfully preserved down through the millennia - where Christians met and worshiped in secret and buried their dead. The most famous and extensive of these are in Rome, but they are also to be found in much more unlikely places, such as the Greek island of Milos.